Go to full page →

ዛሬ የተአምራቶች አስፈላጊነት ለምን አነስተኛ እንደሆነ Amh2SM 54

ክርስቶስ የሰራበት መንገድ ቃሉን ለመስበክና በተአምራዊ የፈውስ ሥራዎች አማካይነት እየተሰቃዩ የነበሩትን ከሥቃያቸው ለማሳረፍ ነበር፡፡ ነገር ግን ሰይጣን ተአምራቶችን በመስራት ኃይሉን ሥራ ላይ ስለሚያውል አሁን በዚህ መንገድ መስራት እንደማንችል መመሪያ ተሰጥቶኛል፡፡ ሀሰተኛ የሆኑ የፈውስ ሥራዎች መለኮታዊ እንደሆኑ እየተነገሩ ስለሚሰሩ ዛሬ የእግዚአብሔር አገልጋዮች በተአምራት አማካይነት መስራት አይችሉም፡፡ {2SM 54.2} Amh2SM 54.2

ከዚህ የተነሳ ሕዝቡ አካላዊ የፈውስ ስራን ቃሉን ከማስተማር ጋር አጣምረው ወደ ፊት የሚቀጥሉበትን መንገድ ጌታ አስምሯል፡፡ የጤና ተቋማት ሊቋቋሙና በእነዚህ ተቋማት ትክክለኛ የሆነ የሕክምና ሚስዮናዊ ሥራ የሚያካሄዱ ሰዎች ሊመደቡ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ ወደ ጤና ተቋማቱ ለሕክምና በሚመጡ ሰዎች ላይ ጥንቃቄ የማድረግ ተጽእኖ ይደረጋል፡፡ {2SM 54.3} Amh2SM 54.3

ለብዙ ነፍሳት የወንጌል የሕክምና ሚስዮናዊ ሥራ እንዲደረግ እግዚአብሔር ያዘጋጀው መንገድ ይህ ነው፡፡ --Letter 53, 1904. {2SM 54.4} Amh2SM 54.4