Go to full page →

የክርስቶስ ትምህርት ግልጽነት GWAmh 27

አንደክርስቶስ ያለ ጠንጌላዊ የለም፡፡ የሰማይ ባሰግርማ ሆኖ ሳለ የእኛን ዝቅተኛ ተፈጥሮ ወሰደ (እኛን መሰለ)። ለሐብታምና ለደሀ፤ ለነፃዓም ሰባሪያም፣ ክርስቶስ የቃል ኪዳን መልዕክትኛ የመዳንን የምሥራች፣ አበሠረ:: የታላቅ ፈዋሽነት ዝናው በፓለስታይን በመሉ ተዳረሰ፡፡ በሸተኞች ሁሉ ዕርዳታውን ለማግኘት በሚሄድበት ሁሉ ይከተሉት ብዙዎቹም ቃሉን ለመስማት ጓጉተው: GWAmh 27.1

በታላላቅ የሕዝብ አውደ ዓመት ይገኝ ነበር፡፡ ለሚሰበስበው ሕዝብ የሰማይን የምሥራች ይናገር ነበር፡፡ ለሁሉም ከጥበብ ጐተራ የዕውቀትን ሀብት ያሠራጭ በሚያስተውሉት ቀላል አነጋገር ያስተምር ነበር፡፡ በሀዘንና በችግር የሚቆራመዱትን ሁሉ የራሱ ብቻ በሆነ ዘዴ አስረዳቸው:: በኃጢዓት የተወጉትን ነፍሳት በትሁት አገልጋይነቱ አረፍት አጐናጸፋቸው፡፡ GWAmh 27.2

የመምህራን ሁሉ የበላይ የሆነው ክርስቶስ በሚያውቁት መንገድ ሰዎችን መራቸው፡፡ ዕውነትን አዳማጮቹ በማይረሱት ቀላል ዘዴ አስተማራቸው፡፡ ማንነቱን አንዲረዱ አድርጐ ከራሱ ጋር በደንብ አስተዋወቃቸው፡፡ ትምህርቱ ቀጥተኛ፤ መግለጫዎቹ ተገቢ፤ ስሜቱ ርህራሄ የተሞላበት ስለነበር አዳማጮች ተደሰቱ፡፡ ግልጽነቱና ዕውነተኛነቱ ለችግረኞች የተናገረውን ቃሉን ቀደሰለት፡፡ GWAmh 27.3