Go to full page →

ሕይወት አደራ ነው MYPAmh 152

ወጣቶች በሕይወታቸው ደስ ያሰኛቸውን የማድረግ ነፃነት እንደሌላቸው እንዲያውቁ ሊደረጉ ይገባል፡፡ አሁን የመታመን ቀን ነው፤ ዋጋቸውን የሚያገኙበት ቀን ይመጣል፡፡ የእርሱን ክቡር ሥጦታዎች አቅልለው በማየታቸው እግዚአብሔር ተጠያቂ ያደርጋቸዋል፡፡ የዓለም አዳኝ ለእነርሱ ገደብ የለሽ ዋጋ ስለከፈለላቸው ሕይወታቸውና መክሊቶቻቸው የእርሱ ናቸው፡፡ በመጨረሻም እግዚአብሔር በአደራ በሰጣቸው ንብረት ላይ ታማኝ በመሆናቸው ወይም ባለመሆናቸው ሁኔታ ይፈረዳሉ፡፡ የተሰጣቸው ንብረትም ሆነ አጋጣሚ ትልቅ በሆነ መጠን ከባድ የሥራ ኃላፊነት እንደተጣለባቸውና የበለጠ እንዲሰሩ እንደሚጠበቅባቸው መማር አለባቸው፡፡ ወጣቶቻችን ለፈጣሪያቸው ያላቸውን ኃላፊነትና በሕይወጣቸው የተሰጣቸውን ጠቃሚ አደራ እንዲሰማቸው ተደርገው ቢያድጉ ኖሮ ብዙ እምነት የሚጣልባቸውን የዘመኑን ወጣቶች እየዋጠ ባለው የእርኩሰትና የወንጀል ሽክርክሪት ውስጥ ለመዘፈቅ አይደፍሩም ነበር፡፡ Review & Herald, Dec 13,1881. MYPAmh 152.6