Go to full page →

ለሚስዮናዊ ሥራ መቆጠብ MYPAmh 194

ምንም እንኳን ደሃ ቢሆን ትጉህ ሰራተኛና ቆጣቢ የሆነ ወጣት ለእግዚአብሔር ስራ ትንሽ መቆጠብ ይችላል። እኔ የአስራ ሁለት ዓመት ልጅ እያለሁ መቆጠብ ምን እንደሆነ አውቄ ነበር። ምንም እንኳን በቀን ውስጥ የምናተርፈው ሃያ አምሰት ሳንቲም ብቻ ቢሆንም ከእህቴ ጋር መነገድን ተምረን ነበር። ከዚያ ላይ ለሚስዮን ስራ ትንሽ መቆጠብ ችለን ነበር። ትንሽ በትንሽ ተጠራቅሞ ሰላሳ ዶላር እስኪሆን ድረስ ቆጥበን ነበር። ያኔ የጌታችን በቶሎ መምጣት መልዕክት የሰዎችንና ለስራው የሚያስፈልጉ ነገሮችን እገዛ ጨምሮ በመጣልን ጊዜ ያንን ሰላሳ ዶላር በበራሪ ጽሁፎችና ፓምፕሌቶች ላይ ውሎ በጨለማ ውስጥ ላሉ ሰዎች መልእክቱን ለመላክ እንዲያገለግል ለአባታችን መስጠታችን እንደ መልካም እድል ተሰማን። MYPAmh 194.3

የእግዚአብሔርን ሥራ የሚነኩ ሁሉ በጊዜና በገንዘብ አጠቃቀም ላይ ቁጠባን መማር ሃላፊነታቸው ነው። ሥራ ፈት ሰዎች ለተሰጡን ክቡር እውነቶች አነስተኛ ቦታ መስጠታቸውን ይገልፃሉ። እነርሱ ተግቶ የመስራትን ልምዶችና ዓይናቸውን በእግዚአብሔር ክብር ላይ በማድረግ መሥራትን መማር አለባቸው። MYPAmh 194.4