Go to full page →

ከፍ ወደለው ደረጃ መድረስ MYPAmh 37

መክሊቶችህ ምንም ያህል ትልቅ ወይም ትንሽ ቢሆኑ ያለህ ነገር ሁሉ ያንተ የሆነው በአደራ መሆኑን አትርሳ፡፡ እግዚአብሔር ራስህን እውነተኛ እንደ ሆንክ እንድታረጋግጥ መልካም አጋጣሚ በመስጠት እየፈተነህ ነው፡፡ ለተሰጡህ ችሎታዎችህ ሁሉ ለእርሱ ባለ እዳ ነህ፡፡ ያንተ የአካል፣ የአእምሮና የነፍስ ኃይሎች የእርሱ ስለ ሆኑ ለርሱ ክብር ጥቅም ላይ መዋል አለባቸው፡፡ ጊዜህ፣ በሌሎች ላይ የምታሳድረው ተጽዕኖህ፣ ችሎታዎችህና ክህሎትህ ለሰጠህ ለእርሱ መቆጠር አለባቸው፡፡ መክሊቶቹን በከፍተኛ ጥረት እግዚአብሔር ሰብዓዊ ዘርን ከውድቀት ለማንሳት ያለውን እቅድ ለመፈፀም የሚሻ ሰው በትክክል እየተጠቀማቸው ነው፡፡ MYPAmh 37.4

በጀመርከው ሥራ ድልን በድል ላይ እስክትቀዳጅ ድረስ ቀጥልበት፡፡ እራስህን ለተግባር አሰልጥን፡፡ ከፍ ያለውን መስፈርት ያውም የእግዚአብሔርን ክብር በማንፀባረቅ ታላላቅ መልካም ነገሮችን እንደምትፈፅም በእይታህ አስቀምጥ፡፡ The Youth’s Instructor January 25, 1910. MYPAmh 37.5