Go to full page →

ኃይማኖት የህሊና ፈጠራ አይደለም MYPAmh 94

ንፁህና ያልረከሰ ኃይማኖት የሰዎች የህሊና ፈጠራ ሳይሆን የምህረትና የፍቅር ሥራን መስራት ነው። ይህ ኃይማኖት ለጤንነትና ለደስታ አስፈላጊ ነው። ወደ ረከሰው የነፍስ ቤተ መቅደስ በመግባት ኃጢአት የሆኑ ጣልቃ ገቦችን በጅራፍ ያባርራቸዋል። ዙፋኑን በመውሰድ ልብን በጽድቅ ፀሐይ ብሩሕ ጮራዎች በማብራት በቦታው በመገኘት ሁሉን ይቀድሳል። የእግዚአብሔር የፍቅሩ ፀሐይ ብርሃን እንዲገባ በማድረግ የነፍስን መስኮቶች ወደ ሰማይ ይከፍታል። ከዚህ ጋር ፅናትና መረጋጋት ይመጣል። የአካል፣ የአእምሮና የግብረገብ ጥንካሬ ይጨምራል። ለዚህም ምክንያቱ የሰማይ ከባቢ አየር እንደ ሕያው የሚሰራ ወኪል ነፍስን ስለሚሞላ ነው። ክርስቶስ በውስጥ የክብር ተስፋ ሆኖ ተመስርቷል። Review & Herald, October 15,1901. MYPAmh 94.4