Go to full page →

የአኗኗር ሳይንስ MYPAmh 152

ትውልዳችንን ወደ ውድመትና ሞት ጠራርጎ እየወሰደ ያለውን የበሽታና የወንጀል ማዕበል ለማገድ ምን ማድረግ ይቻላል? የክፉው ታላቁ ሥራ ያለው የምግብ ፍላጎትን ባለመቆጣጠርና በፍትወት ውስጥ ስለሆነ የመጀመሪያው ታላቁ የተሃድሶ ሥራ መሆን ያለበት መሻትን የመግዛትና ራስን የመቆጣጠር ትምህርቶችን መማርና መለማመድ ነው፡፡ MYPAmh 152.1

ለህብረተሰብ ጥቅም ቋሚ ለውጥ ለማምጣት ሕዝብን የማስተማር ሥራ በልጅነት ጊዜ መጀመር አለበት፡፡ በልጅነትና በወጣትነት ጊዜ የተመሠረቱ ልምዶች፣ በልምድ የተገኙ ምርጫዎች፣ የተገኙ ራስን የመግዛት ችሎታዎች፣ በሕጻን አልጋ ላይ እያሉ የጎለበቱ ሥነ ሥርዓቶች የአንድን ወንድ ወይም ሴት የወደፊት ሕይወት የሚወስኑ መሆናቸው እርግጥ ነው፡፡ መሻትን ባለመግዛትና በግብረገብ ልቅነት የሚገለጹ ወንጀልና ሙስናን ወጣቶችን በአግባቡ በማሳልጠን መከላከል ይቻል ነበር፡፡ MYPAmh 152.2