Go to full page →

የብቃታችን ምንጭ MYPAmh 29

ጉልበታቸውን ለሥራ ለማዋል የማይፈሩና ታማኝነት ያለበትን ሥራ የሚሰሩ ወጣቶችን መጠቀም አለብን፡፡ እንደ እነዚህ ዓይነት ወጣቶች በመንገድ ላይ የማያመነቱ ስለ ሆኑ በማንኛውም ሥፍራ ሃላፊነት ሊሰጣቸው ይችላል፡፡ ዓይናቸው በአንድ አቅጣጫ ያተኮረ ስለ ሆነ የድል ጩኸት እያሰሙ ወደፊትና ወደ ላይ ያለ ማቋረጥ ይገፋሉ፡፡ ነገር ግን ለቸልተኞች፣ ለፈሪዎችና ለማያምኑ እንዲሁም በእምነት-የላሽነታቸውና ስለ ክርስቶስ ብለው ራሳቸውን ለመካድ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ምክንያት ሥራው ወደ ፊት እንዳይገሰግስ የሚያግዱ ጥሪ የላቸውም፡፡… MYPAmh 29.5

እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር አብረው የሚሰሩትን ይጠራል፡፡ ከክርስቶስ ጋር ሲገናኝ የሰው ተፈጥሮ ንፁህና ትክክለኛ ይሆናል፡፡ ክርስቶስ ብቃትን ይሰጥና ሰው የመልካም ኃይል ምንጭ ይሆናል፡፡ እውነተኛነትና ለእውነት ፀንቶ መቆም የእግዚአብሔር ባህሪያት ስለሆኑ እነዚህ ባህሪያት ያለው ሰው የማይሸነፍ ኃይል ይኖረዋል፡፡ Review and Herald, March 10,1903. MYPAmh 30.1