Go to full page →

የዘላለማዊ አምላክ ድምፅ MYPAmh 173

በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ አእምሮን ለጠለቀ አስተሳሰብና ከፍ ላለ ጥረት የሚገፋፋ ጉዳይ ይገኝበታል። በቃሉ ውስጥ ከአቦውና ከነቢያት ጋር ግንኙነት ታደርጋላችሁ! ዘላለማዊ አምላክ ለሰዎች ሲናገር ድምጹን ትሰማላችሁ:: እዚህ የሰማይ ንጉሥ የእኛ ምትክና ዋስ ለመሆን ራሱን ዝቅ ሲያደርግ፣ በእኛ ፈንታ ድል ለማድረግ ከጨለማ ሠራዊት ጋር ብቻውን ሲጋፈጥ ታያላችሁ:: በእንደዚህ ዓይነት ጉዳዮች ላይ በአክብሮት ማሰላሰል ልብን ሳያለሰልስ፣ ሳያነፃና የከበረ ሳያደርግ እንደዚሁም አእምሮን በአዲስ ኃይልና ብርታት ሳይሞላ አይቀርም። MYPAmh 173.2

እግዚአብሔር እንዲፈፅሙ የሚጠብቅባቸውን ነገሮች በግድየለሽነትና በንቀት መመልከትን እንደ ጉብዝና እና ወንድነት የሚቆጥሩ ሰዎች የራሳቸውን ሞኝነትና ድንቁርና እያጋለጡ ነው። በነፃነታቸውና ከጥገኝነት ነፃ በመሆናቸው የሚኮሩ በኃጢአትና በሰይጣን ግዞት ውስጥ ናቸው። MYPAmh 173.3