Go to full page →

ፈውሱ MYPAmh 183

ክፉ እንዳይበቅል (እንዳያድግ) ለመከላከል የተሻለው መንገድ አስቀድሞ መሬቱን ማስያዝ ነው። አእምሮን መኮትኮትና በዚያው ውስጥ ውድ የሆኑ የጽሐፍ ቅዱስ እውነቶችን በመዝራት ሂደት ታላቅ ጥንቃቄና ነቅቶ መጠበቅ ያስፈልጋል። ጌታ በታላቅ ምህረቱ በቃሉ ውስጥ የተቀደሰ አኗኗር ህጎችን ገልጦልናል……። MYPAmh 183.5

ጌታ በመንገዳችን ሊገጥሙን የሚችሉ አደጋዎችን በተመለከተና እነዚህን አደጋዎች እንዴት ማምለጥ እንደሚቻል የሚገልፁ መመሪያዎችን ለጥቅማችን እንዲጽፉ ቅዱሳን ሰዎችን መርቷቸዋል። መጻሕፍትን እንዲመረምሩ የተሰጣቸውን ትዕዛዝ የሚታዘዙ ሰዎች ስለነዚህ ጉዳዮች መሃይማን አይሆኑም። በመጨረሻው ቀናት አደጋዎች ውስጥ እያንዳንዱ የቤተክርስቲያን አባል ለመገንዘብ ከባድ ያልሆኑትን የተስፋውንና የእምነቱን ምክንያቶች ማስተዋል አለበት። በፀጋና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት የምናድግ ከሆነ አእምሮን ለመያዝ የሚችል በቂ የሆነ ነገር አለ። Christian Temperance and Bible Hygiene, P. 123-126 (1890). MYPAmh 183.6