Go to full page →

ራስን ማስደሰት MYPAmh 204

የህዝባችንን ቤቶችና ት/ቤቶቻችንን ስጎበኝ በጠረጴዛዎች ላይ ያለው ቦታ በሙሉ፣ ተራ በሆኑ ነገሮች፣ ግርግዳዎቻቸው በሙሉ በፎቶግራፎች ተሞልቶ አያለሁ። በግራና በቀኝ የሰው ፊት የሚያሳዩ ፎቶዎች ይታያሉ። እግዚአብሔር የዚህ አይነት ነገሮች እንዲለወጡ ይፈልጋል። ክርስቶስ በምድር ላይ ቢሆን ኖሮ እንዲህ ይል ነበር፡- “እነዚህን ነገሮች ከዚህ ውሰዱአቸው።” እነዚህ ፎቶዎች እንደ ብዙ ጣኦቶች በመሆን ለእግዚአብሔር በቅድስና ሊሰጡ የሚችሉትን ጊዜና አሳብ የሚወስዱ እንደሆኑ ተነግሮኛል። MYPAmh 204.1

እነዚህ ፎቶዎች ገንዘብ ያስወጣሉ። በዚህ ሰዓት ሊሰራ የሚገባውን ሥራ እያወቅን የራሳችንንና የጓደኞቻችንን ፊት የሚያሳዩ ፎቶዎችን ለማምረት የእግዚአብሔርን ገንዘብ ወጪ ማድረግ ለእኛ ተገቢ ነውን? እያንዳንዱ መቆጠብ የምንችለው ብር የእግዚአብሔርን ሥራ ለመገንባት ሥራ ላይ መዋል የለበትምን? እነዚህ ፎቶዎች ለእግዚአብሔር አገልግሎት ተቀድሶ ሊሰጥ የሚችለውን ገንዘብ ይወስዳሉ። እንደዚሁም አእምሮን ከእግዚአብሔር ቃል እውነቶች ይመልሳሉ። MYPAmh 204.2