ለወጣቶች ጥልቅ ፍላጎት ስላለኝ የክርስቲያን ባህሪያትን ለመገንባት ቃሉን ተግተው በማጥናትና ልባዊ በሆነ ፀሎት በእግዚአብሔር ሥራ ውስጥ ተቀባይነት ያለው አገልግሎት ለማበርከት የሚያስችል ሥልጠና እንዲኖራቸው ሲጥሩ ለማየት እጅግ እጓጓለሁ:: እጅግ ከፍ ወዳለው ክርስቲያናዊ ልምምድ ለመድረስ እርስበርስ ሲረዳዱ ለማየት እጓጓለሁ:: MYPAmh 18.1
ክርስቶስ የመዳን መንገድ በመሆን ሰብዓዊ ዘርን ለመድረስ መጣ:: በዚህም የደህንነትን መንገድ ትንሽ ህፃን እንኳን ሊሄድበት እንዲችል አድርጎ አስተካከለው:: ተከታዮቹን ጌታን ለማወቅ እንዲከተሉት ይጠይቃል:: እነርሱም በየቀኑ የእርሱን አመራር ሲከተሉ አወጣጡ እንደ ንጋት የተዘጋጀ መሆኑን ይማራሉ:: MYPAmh 18.2
ማለዳ የፀሐይን መውጣትና ቀስ በቀስ በምድርና በሰማይ ላይ ሙሉ የቀን ብርሃን ሲሆን አይታችኋል:: ቀስ በቀስ ፀሐይ እስክትወጣ ድረስ ንጋት ይጨምራል:: ከዚያም እስከ እኩለ ቀን ሙሉ ግርማ እስኪደርስ ድረስ ብርሃኑ ያለማቋረጥ እየጨመረ” እየጠነከረና እየጠራ ይሄዳል:: ይህ እግዚአብሔር የልጆቹን ክርስቲያናዊ ልምምድ ፍፁም ለማድረግ ያለው ፍላጎት ውብ መግለጫ ነው:: እርሱ የሚፈለግብንን ሁሉ ለማድረግ በፍላጎታችን በመታዘዝ በየቀኑ በሚልክልን ብርሃን ስንሄድ ክርስቲያናዊ ልምምዳችን በክርስቶስ የሱስ ሙሉ ሰዎች ወደ መሆን እስክንደርስ ድረስ እያደገና እየሰፋ ይሄዳል:: MYPAmh 18.3
ወጣቶች ሁል ጊዜ የሱስ የተከተለውን መንገድ በፊታቸው ማኖር ያስፈልጋቸዋል:: ክርስቶስ በያንዳንዱ እርምጃ የሄÅበት መንገድ የድል መንገድ ነበር:: ክርስቶስ ወደዚህ ምድር የመጣው ህዝቦችን ለመግዛት ንጉስ ሆኖ አልነበረም:: •እርሱ የመጣው ትሁት ሰው ሆኖ ለመፈተንና ፈተናን ለማሸነፍ እንዲሁም እኛ እግዚአብሔርን ለማወቅ መከተል የሚገባንን መንገድ ለመከተል ነበር:: MYPAmh 18.4
የየሱስን ህይወት ስናጠና እግዚአብሔር በእርሱ አማካይነት ለልጆቹ ምን ያህል እንደሚያደርግልን እንማራለን:: እንደዚሁም ፈተናዎቻችን የፈለገውን ያህል ትልቅ ቢሆኑም የሱስ ለኛ ከተሸከመው መከራ እንደማይበልጡ እንማራለን:: መንገድ ” እውነትና ህይወትም እርሱ መሆኑን እንድናውቅ ይረዱናል:: ከእርሱ የሕይወት ምሳሌ ጋር የተጣጣመ ህይወት በመኖር ለኛ የከፈለውን መስዋዕትነት ማድነቃችንን ማሳየት ይጠበቅብናል:: MYPAmh 18.5
ወጣቶች ሥፍር በሌለው በእግዚአብሔር ልጅ ደም ተገዝተዋል:: አብ ልጁ ይህንን መስዋዕትነት እንዲከፍል የመፍቀዱን መስዋዕትነት ልብ ይበሉ:: የሱስ ህይወቱን ለሰብዓዊ ዘር የየዕለት መስዋዕት አድርጎ ለመስጠት የሰማይን አደባባዮችና ዙፋን ትቶ ሲወጣ የተወውን ሁሉ ልብ ይበሉ፡፡ ፌዝና ልግጫ ደርሶበታል:: ክፉ ሰዎች ሊጭኑበት የሚችሉትን ስድብና ፌዝ ሁሉ ተሸከመ፡፡ ምድራዊ አገልግሎቱ እንደተጠናቀቀም በመስቀል ተሰቅሎ ሞቷል:: እጆቹና እግሮቹ በምስማር ሲቸነከሩ፤ ሊያድናቸው ከመጣላቸው ሰዎች የሚደርስበት ፌዝና ድብደባ፣ አባቱ ፊቱን ሲያዞርበት በመስቀል ላይ የደረሰበትን ህመምና ሥቃይ አስታውሱ:: ነገር ግን የሱስ ይህንን ሁሉ በማድረግ ፈቃደኛ ለሆኑ ሁሉ የአምላክን ህይወት በሚያክል ዋጋ ህይወት እንዲያገኙ አስቻለ:: MYPAmh 18.6