Go to full page →

አገልግሎት በተለያየ ዘርፍ MYPAmh 137

እግዚአብሔር አገልጋዮችን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ሠራተኞችንና መጽሐፍት ሻጮችን ይጠራቸዋል፡፡ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችን እንደ መጽሐፍት ሻጮች፣ እንደ ወንጌላውያንና የመጽሐፍ ቅዱስ ሠራተኞች እንዴት በተሳካ ሁኔታ ሥራቸውን መስራት እንዳለባቸው ሊያሳዩአቸው ከሚችሉ ልምድ ካላቸው ሠራተኞች ጋር ለሥራ ይሂዱ፡፡ መጽሐፍት ሻጮች ከቤት ወደ ቤት ይወሰዱ፡፡ አጋጣሚውን ሲገኙ ለሚያገኙአቸው ሰዎች የወቅቱን እውነት ይንገሩአቸው፡፡ ከእነርሱ ጋር አብረው ይፀልዩ፤ ይዘምሩ፡፡ ለእግዚአብሔር የምንሰራው ስራ ትክክለኛ ዘዴዎችን በኃይል ብንከተል የነፍሳት መከርን እንሰበስባለን፡፡ MYPAmh 137.1

ራስን በመሰዋት መንፈስ ለተሞሉ ሁሉ በእግዚአብሔር ሥራ ውስጥ ቦታ አለ፡፡ እግዚአብሔር ለሌሎች ሲሉ ራሳቸውን ለመካድ ፈቃደኛ የሆኑና ያላቸውን ነገር ሁሉ ለሥራው የሚቀድሱትን ወንዶችና ሴቶች እየጠራቸው ነው፡፡ ችግር ሲገጥማቸው አንወድቅም፣ ተስፋም አንቆርጥም በማለት ያለ ማቋረጥ ወደ ፊት የሚያጠናክሩና የሚገነቡ ሰዎች ይፈለጋሉ፡፡ Review and Herald, April 28, 1904. MYPAmh 137.2