Go to full page →

ወጀቡ እየመጣ ነው MYPAmh 63

ወደ እግዚአብሔር በንስሐ በመቅረብና በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የወጀቡን ቁጣ ለመጋፈጥ መዘጋጀት አለብን፡፡ ጌታ ምድርን በአሰቃቂ ሁኔታ ሊያናውጣት ይነሳል፡፡ ችግሮችን በሁሉም አቅጣጫዎች እናያለን፡፡ በሺሆች የሚቆጠሩ መርከቦች ወደ ባህር ጥልቀት ይወረወራሉ፡፡ የባህር ኃይሎች ይሰምጡና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰብዓዊ ሕይወቶች ይሰዋሉ፡፡ ማንኛውም ሰብዓዊ ጥረት ሊያጠፋቸው የማይችሉ የሰደድ እሳቶች በድንገት ይነሳሉ፡፡ ምድራዊ ቤተመንግስቶች በእሳቱ የቁጣ ነበልባል ይወድማሉ፡፡ በሐዲድ ባቡር የሚደርሱ አደጋዎች ቶሎ ቶሎ ይከሰታሉ:: ግራ መጋባት፣ ግጭትና ያለ አንዳች ማስጠንቀቂጣ የሚመጣ ሞት በታላላቅ የመጓጓዣ መስመሮች ላይ ይከሰታል፡፡ ፍፃሜው ቅርብ ነው፤ የምህረት በር እየተዘጋ ነው፡፡ እግዚአብሔርን በሚገኝበት ጊዜ እንፈልገው፤ ቀርቦ ሳለም እንጥራው፡፡ ነቢዩ «የምድር ትሁታን ፍርድን ያደረገውን ጌታ ፈልጉ፤ ጽድቅን እሹ፣ ትህትናን ፈልጉ፤ ምናልባት በጌታ የቁጣ ቀን ትሰወሩ ይሆናል»ብሏል ፡፡ The signs of the times, April 21,1890. MYPAmh 63.2