Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents

ቀደምት ጽሑፎች

 - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    12—በመከራው ወቅት መደረግ ያለባቸው ተግባራት

    በመከራው ወቅት ሊያስፈልጉን ለሚችሉ ጊዜያዊ ነገሮች ስንቅ ማዘጋጀት ከመጽሐፍ ቅዱሳዊው ጽንሰ ሃሳብ ጋር የሚጋጭ መሆኑን ጌታ በተደጋጋሚ አሳይቶኛል:: ቅዱሳኑ ያከማቹት ምግብ ወይም በመስክ ላይ የተሰበሰበ እህል ቢኖር ሠይፍ፣ ረሃብና ቸነፈር በምድሪቱ ላይ በተንሰራፉ ጊዜ በጸንፈኛ እጆችና በባዕዳን ሰዎች ከእነርሱ ይወሰዳሉ ይህ በእግዚአብሔር ሙሉ ለሙሉ ልንታመን የሚገባን ወቅት ይሆናል እርሱም ደግፎ ይይዘናል:: በያን ጊዜ የምንበው ዳቦና የምንጠጣው ውሃ የታመነ እንደሚሆን ተመልክቼአለሁ:: እግዚአብሔር በምድረበዳ ማዕድ ሊያዘጋጅልን ስለሚችል በያን ጊዜ በእጦት ወይም በረሃብ አንሰቃይም አስፈላጊ ከሆነ ለኤልያስ እንዳደረገው ቁራዎችን በመላክ ይመግበናል ወይም ለእስራ ኤላውያኑ እንደሆነው ከሰማይ መና ያንብልናል። EWAmh 39.1

    በመከራው ጊዜ ቤትና ቦታ ለቅዱሳኑ የሚሰጡት ጥቅም አይኖርም ምክንያቱም በዚያን ወቅት በቁጣ ከፈሉ ሰዎችን አድማ መሸሽ ይኖርባቸዋል: ደሞም ያን ጊዜ ወቅታዊው እውነት ወደፊት ይገሰግስ ዘንድ ንብረቶቻቸው መሸጥ አይችሉም የመራው ጊዜ ከመምጣቱ አስቀድሞ ቅዱሳኑ ከማንኛውም እንቅፋት ከሚሆኑ ነሮች ተቆርጠው መለየትና መስዋዕት በማቅረብ ኪዳን መግባታቸው የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆን ተመልክቼ ነበር: ንብረቶቻቸውን በመሰዊያው ላይ በማስቀሙጥ ምን ማድረግ እንዳለባቸው እግዚአብሔርን በጽናት ቢጠይቁት ንብረቶቻቸውን መቼ መሸጥ አንዳለቸ ያወቃቸዋል:: ይህ ሰሆን በወ ዝ ቈልቁል የጫናቸ ነር አይኖርም: EWAmh 39.2

    ንብረቶቻቸውን የሙጥኝ ብለው በመያዝ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ጌታን ላልጠየቁ ለማናቸውም ማድረግ ያለባቸውን ግዴታ ይፋ እንደማያደርግላቸው ተመልክቼአለሁ:: በዚህም ንብረቶቻቸውን እንደጠበቁ እንዲይዙ በሚያገኙት ፈቃድ ንብረታቸው በመከራው ጊዜ እንደሚጨፈልቅ ተራራ ሆኖ ይመጣበቸዋል: ለመሸጥ ሙከራ ቢያደርጉም ነገር ግን አይችሉም:: አንዳንዶች እንዲህ ብለው ሲያቡ ሰምቼ ነበር ሥራው እየተዳከመ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ደግሞ እውነትን እየተጠሙ ነበር እኛም የበረውን ጉድeት ለመሙላት ያደረግነው አንዳችም ጥረት አልነበረም: አሁን ንብ ረቶቻችን ሁሉ ዋጋ ቢስ ሆነዋል:: ምናለ ቀደም ብለን ሸጠን ሐብታችንን በሰማይ ባከማቸን ይቀርብ የነበረው መስዋዕት እንዳልጨመረ ይልቁንም እየቀነሰ እንደነበር ተመልክቻለሁ: እንዲሁም ሁሉም ሕዝቡ ንብረቱን በተመሳሳይ ወቅት ይሸጥ ዘንድ እግዚአብሔር እንዳልጠየቀ ተመልክቼ ነበር:: ነገር ግን እነዚህ ሕዝቦች ለመማር ምኞት ካቸው ያስተምራቸው ነበር:: እንዲሁም አስፈላጊ በሆነ ጊዜ መቼና በምን ያህል ዋጋ መሸጥ እንዳለባቸው ያሳውቃቸው ነበር የዳግም ምጽአቱን መልእክት ለመደገፍ ያስትል ዘንድ ጥቂቶች ንበረቶቻቸውን ወደ ኋላ ባሉት ጊዜያት እንዲሸጡ ተጠይቀው የነበረ ሲሆን ሌሎች ደግሞ አስፈላጊ አስከሆበት ጊዜ ደረስ እንዲያቆዩ ተፈቅዶላቸው ነበር: ከዚያም ለሥራው እንዳስፈለገ የእነርሱ ተግባር መሸጥ ነበር። EWAmh 39.3

    «ያwህን ሸጠህ ለድኾች መጽውት, የተሰኘው የአዳኙ ተጨባጭ መልእክትግልጽ ሆኖ ባለመቅረቡ—በአንዳንዶች ግልጽ በሆነ ብርሃን አልተሰጠም ነበር: የመሸጥ ዓላማ መሥራትና እራሳቸውን መርዳት ለሚችሉት ለመመጽወት ሳይሆን ነገር ግን እውነትን ለማስራጨት ነው: መሥራት እየቻሉ እጆቻቸውን አጣጥፈው የተቀመጡትን መደገፍ ኃጢአት ነው:: አንዳንዶች በእያንዳንዱ ጉባዔ ለመካፈል የጋለ ስሜት ቢኖራቸውም ነገር ግን ይህን የሚያደርገት ለእግዚአብሔር ክበር ለመስጠት ሳይሆን ‹ለዳቦና ዓሣ» ሲሉ ነው: እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች «መልካም የሆነውን ሁሉ በእጆቻቸው ቢሠሩና ለቤተሰባቸው የሚያስፈልገውን ቢያሟሉ እንዲሁም የከበረውን ውቅታዊ መልእክት የሚደግፉበት ጥቂት ነገር ቢኖራቸው በእጅጉ የተሻለ ይሆናል: ለመከራው ጊዜ በመጋጀተበሰማይ ሐብት የምናከማችበትና ልባችንን በዚያው የምናደርግበት ጊዜው አሁን ነው:: ንጹህ እጆችና ንጸህ ልቦች ያሏቸው እነርሱ ብቻ በዚያ የፈተና ወቅት ጸንተው ይቆማሉ: የእግዚአብሔር ሕግ በአእምሮአችን፣ በግንባራችንና በልባችን የሚጻፍበት ጊዜ እነሆ አሁን ነው: EWAmh 40.1

    አእምሮአችን በምድራዊው አስተሳሰብና ጥንቃቄ እንዲሞላ የመፍቀዱን አደጋ ጌታ አሳይቶኛል: አንዳንድ አእምሮዎች አስደሳች ያሏቸውን ሌሎች መጻሕፍትን በማንበብ ከወቅታዊው እውነትና ከመጽሐፍ ቅዱስ ፍቅር ተነድተው ሲወጡ የተመለከትኩ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ምን እንደሚበሉ፣ ምን እንደሚጠጡና ምን እንደሚለብሉ ሲጨነቁ አይቻ ለሁ: ጥቂቶች ጌታ ዳግም ይገለጣል ብለው ከጠበቁት ጊዜ ተጨማሪ ጥቂት ዓመታት በማለፋቸው ዳግም ምጽአቱ ገና ብዙ ጊዜያት እንደሚወስድ በማሰብ እሩቅ አድርገው ይመለከቱ ነበር: ነገር ግን በመሃል አእምሮአቸው ከወቅታዊው እውነት በማፈንገጥ ዓለምን ተከትሎ ነጎደ: በዚህ ዙሪያ ታላቅ አደጋ የተመለከትኩ ሲሆን ይኸውም አእምሮ በሌሎች ነገሮች ከተሞላ ለወቅታዊው እውነት የተጋ ይሆናል—ይህን ተከትሎ የሕያው እግዚአብሔርን ማኅተም በግንባሮታችን ላይ የምንታተምበ ቦታ አይኖርም: የሱስ በቅድስተቅዳሳኑ ክፍል የሚቆLበት ጊዜ እያለቀ መሆኑን ተመልክቻለሁ: ባሉን ትርፍ ጊያቶች ሁሉ በመጨረሻው ቀን የምንዳኝበተን—መጽሐፍ ቅዱስ በማንበብ ልናጠፋው ይገባል፡፡ EWAmh 40.2

    የተወደዳችሁ ወንድምና እህቶቼ የእግዚአብሔር ትእዛትና የየሱስ ክርስቶስ ምስክር ያለማቋረጥ በአእምሮቸችሁ ውስጥ በመሆን ዓለማዊ አስተሳቦችንና ጥንቃቄ ዎችን ጠራርገው ያውጧቸው:: ስትተኙም ሆነስትነሱ ጸሎታችሁ ይኸው ይሁን:: አኗኗራችሁና ድርጊቶቻችሁ የሚመጣውን የሰው ልጅ የተቀደሰ ማንት ምሳሌ ያደረገ ይሁን: የምንታተምበት ጊዜ በጣም ኣጭርና በቅርቡ የሚያበቃ ነው:: የተጠራንበትንና የተመረጥንበትን የምንተገብረው አራቱ መላእክት አራቱን ነፋሳት በያዙበት እነሆ በአሁኑ ወቅት ነው:: EWAmh 40.3

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents