Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents

የልጅ አመራር

 - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    ክፍል 11—የተሳሳተ እርማት

    ምዕራፍ 46—አግባብነት የሌላቸው ምኞቶችን የማርካት ክፋቶች

    እውነተኛ ፍቅር አግባብነት የሌላቸውን ምኞቶችን ማርካት አይደለም— ፍቅር ለልጆች ልብ ቁልፍ ነው፣ ነገር ግን ወላጆች የልጆቻቸውን ሕገ-ወጥ ምኞቶችን እንዲያረኩ የሚመራቸው ፍቅር ለጥቅማቸው የሚሰራ ፍቅር አይደለም፡፡ የሱስን ከመውደድ የሚመነጭ ጥልቅ ፍቅር ወላጆች ሕጋዊ ስልጣንን እንዲተገብሩ እና ፈጣን ታዛዥነትን መስፈርት እንዲያደርጉ ያስችላቸዋል፡፡ እንደ ቤተሰብ ጥበብ፣ በጎነት፣ ትዕግሥት፣ ርህራሄ እና ፍቅር የሚፈስበት መስመር እንዲሆኑ የወላጆች እና የልጆች ልብ አንድ ላይ መጣበቅ አለባቸው። 528The Review and Herald, June 24, 1890.CGAmh 255.1

    እጅግ ብዙ ነፃነት የባከኑ ልጆችን ያፈራል— ልጆች እግዚአብሔርን የማይመስሉበት ምክንያት ብዙ ነፃነት ስለሚሰጣቸው ነው፡፡ ፍላጎታቸው እና ዝንባሌዎቻቸው እንዲረካ ይደረጋል…፡፡ አያሌ ብኩን ልጆች አንዲህ የሚሆኑበት ምክንያት ቤት ውስጥ ስለሚያሞላቅቋቸው፣ ወላጆቻቸው የቃሉ አድራጊዎች ባለመሆናቸው ነው፡፡ አዕምሮ እና ዓላማ በጽኑ፣ በማያወላውል፣ በተቀደሱ መርሆዎች የተጠበቁ መሆን አለባቸው፡፡ ወጥነት እና ፍቅር በፍቅር እና በወጥነት ምሳሌ መጎልበት አለባቸው።2Letter 117, 1898.CGAmh 255.2

    ማሞላቀቅ በበዛ ቁጥር፣ ማስተዳደር ከባድ ይሆናል— ወላጆች፣ ቤት ለልጆቻችሁ አስደሳች እንዲሆን አድርጉ፡፡ ይህ ማለት አሞላቅቋቸው ማለት አይደለም፡፡ ይበልጥ በተሞላቀቁ ቁጥር፣ እነርሱን ለማስተዳደር ይበልጥ ከባድ ይሆናል፣ ወደ አለም ሲወጡም እውነተኛ ሕይወት፣ የከበረ ሕይወት ለመኖር ይከብዳቸዋል፡፡ የፈለጉትን እንዲያደርጉ ከፈቀዳችሁላቸው ንፁህነታቸው እና የባህሪያቸው ተወዳጅነት በፍጥነት ይደበዝዛል፡፡ እንዲታዘዙ አስተምሯቸው። የእናንተ ስልጣን መከበር እንዳለበት ይገንዘቡ፡፡ ይህ አሁን ጥቂት ደስታ ሊያሳጣቸው ይችላል፣ ነገር ግን ለወደፊቱ ከብዙ ሐዘን ያድናቸዋል። 529Manuscript Releases 2:1903.CGAmh 255.3

    ልጅን በልጅነቱ እና ስህተት በሚሰራበት ጊዜ ማሞላቀቅ ኃጢአት ነው። ልጅ በቁጥጥር ስር መሆን አለበት።530 Letter 144, 1906. CGAmh 256.1

    ልጆች የራሳቸው መንገድ እንዲኖራቸው ከተፈቀደላቸው ከሚፈለገው በላይ መጠበቅ፣ እንክብካቤ ማግኘት፣ መሞላቀቅ፣ እና መፈንደቅ እንዳለባቸው ያስባሉ። ምኞታቻቸው እና ፍላጎታቸው የግድ መርካት እንዳለበት ያስባሉ፡፡531Manuscript Releases 2:7, 1896. CGAmh 256.2

    እርሷ [እናት] ልጅዋ በተደጋጋሚ የራሱ የሆነ መንገድ እንዲኖረው፣ እንደፈለገ እንዲሰራ፣ ታዛዥ እንዳይሆን ትፈቅድለታለችን? በእርግጠኝነት አይደለም፣ ምክንያቱም ልክ ይህን ስታደርግ፣ ሰይጣን በቤቷ ውስጥ ገሃነማዊ ሰንደቅ ዓላማ እንዲተክል ታደርገዋለች። ለራሱ መጋደል የማይችለውን የዚያን ልጅ ገድል መጋደል አለባት፡፡ ዲያቢሎስን መገሠጽ፣ እግዚአብሔርን በጥብቅ መሻት፣ እና ሰይጣን ልጁን ከእቅፏ አውጥቶ በራሱ እቅፍ እንዳያደርግ ፈጽሞ አለመፍቀድ፣ ያ ስራዋ ነው። 532Manuscript Releases 7:0, Undated.CGAmh 256.3

    ማሞላቀቅ ቁንጥንጥነትን እና አለመርካትን ያስከትላል— በአንዳንድ ቤተሰቦች ውስጥ የልጅ ምኞት ህግ ነው። እርሱ የሚሻው ሁሉ ይሰጠዋል፡፡ የሚጠላውን ሁሉ እንዲጠላ ይበረታታል፡፡ እነዚህን አግባብነት የሌላቸው ምኞቶች እንዲረኩ የሚደረጉት ህፃናትን ለማስደሰት በማሰብ ነው፣ ነገር ግን እርሱን ቁንጥንጥ፣ የማይደሰት እና በምንም እንዳይረካ የሚያደረጉት እነዚህ ነገሮች ናቸው፡፡ ማሞላቀቅ ቀላል እና ጤናማ ምግብን፣ ቀላል እና ጤናማ የጊዜ አጠቃቀምን አባላሽቷል፤ አግባብነት የሌላቸውን ፍላጎቶቹን ማርካት ለጊዜያዊውም ሆነ ለዘለአለማዊው ሕይወት የሚያበቃውን ያ ባህሪይው መሰረት እንዳይይዝ ያደርጋል።7Manuscript Releases 12:6, 1897.CGAmh 256.4

    አክብሮት ለሌላቸው ልጆች የኤልሳዕ ፍቱን ተግሣጽ— ለጠማማ ልጆች መገዛት አለብን የሚለው አስተሳሰብ ስህተት ነው፡፡ በሥራው ጅማሮ ላይ ኤልሳዕ በቤቴል ወጣቶች ተሾፈበት፣ ተፌዘበትም። እርሱ ታላቅ ጨዋነት ያለው ሰው ነበር፣ ነገር ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእነዚያ አናዳጆች ላይ እርግማንን እንዲናገር ገፋፋው፡፡ እነርሱ ስለ ኤልያስ ዕርገት ሰምተው ነበር፣ ይህንንም ክቡር ክስተት የፌዝ ርዕሰ ጉዳይ አደረጉት፡፡ ኤልሳዕ በቅዱሱ ጥሪው ላይ ጎልማሳውም ሆነ ወጣቱ ሊሳለቅበት እንደማይባው አስመሰከረ፡፡ በኤልያስ በእርሱ ፊት እንዳደረገው ሁሉ እርሱም ማረግ ይሻለው እንደነበረ በነገሩት ጊዜ፥ በእግዚአብሔር ስም ረገማቸው። በእነርሱ ላይ የመጣው አሰቃቂ ፍርድ ከእግዚአብሔር ነበር።CGAmh 256.5

    ከዚህ በኋላ ኤልሳዕ ተልእኮው ላይ ሌላ ችግር አልገጠመውም፡፡ ለሃምሳ ዓመት ያህል እጅግ ክፉ፣ ብልሹ፣ ስራ ፈት እና ወራዳ ሕይወት የሚመሩ እጅግ ብዙ ወጣቶች መካከል አየተላለፈ በቤቴል በር ይገባና ይወጣ፣ ከአንዱም ከተማ ወደ ሌላ ከተማ ይዘወር ነበር፤ ነገር ግን ማንም ሰው አላፌዘበትም ወይም የልዑል ነቢይ በመሆኑ ማንም አላቃለለውም፡፡ 533Testimonies For The Church 5:44.CGAmh 257.1

    ለማባባል እጅ አትስጡ— ወላጆች ልጆቻቸው ላይ አግባብነት የሌላቸውን ፍላጎቶችን በማርካት ክፋት የተነሳ በፍርድ ቀን መልስ የሚሰጡባቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ብዙዎች ምክንያታዊ ያልሆኑ ምኞትን ሁሉ ያረካሉ፣ ምክንያቱም ውትወታቸውን ከየትኛውም ሌላ መንገድ በተሻለ በዚህ መንገድ ማስወገዱ ቀላል ስለሆነ ነው። ልጅ እምቢታን በቀና መንፈስ እና እንደ ፍጻሜ መቀበል በሚያስችለው መንገድ መሰልጠን አለበት፡፡ 534Pacific Health Journal, May, 1890.CGAmh 257.2

    የአንዱን ልጅ ቀል በሌሎች ሰዎች በፊት አታንሱ— ወላጆች የልጆቻቸውን ኃጢአት በቀላሉ ማለፍ የለባቸውም፡፡ እነዚህ ኃጢአቶች በአንዳንድ ታማኝ ወዳጆች ሲጠቆሙ ወላጅ መብቱ እንደተወሰደበት፣ በራሱ ላይ ጥቃት እንደተፈጸመበት ሊሰማው አይገባም፡፡ የእያንዳንዱ ወጣት እና እያንዳንዱ ልጅ ልማዶች የህብረተሰቡን ደህንነት ይነካል። የአንድ ወጣት የተሳሳተ አካሄድ ሌሎች ብዙ ወጣቶች ወደ ክፉ መንገድ ሊወስዳው ይችላል። 535The Review and Herald, June 13, 1882.CGAmh 257.3

    የልጆቻችሁን ንግግር በጎልማሶች ክርስቲያኖች ንግግሮች ፊት ስታነሱ እንዲያዩአችሁ አትፍቀዱ። ትልቅ ጉዳት አታደርሱባቸውም፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናቸውን መረጃ ያሉኝን ሰዎች ከማመኔ በፊት ልጆቼን አምናለሁ በማለታችሁ፣ የውሸት ልማድን በውስጣቸው ታበረታታላችሁ። 536The Review and Herald, April 13, 1897.CGAmh 257.4

    የብልሹ ልጅ ውርስ— ልጅን ለራሱ ፍላጎት መተው የሚመጣውን ክፋት ማሳየት አይቻልም፡፡ በልጅነታቸው ጊዜ በደረሰባቸው ቸልተኛነት ሳቢያ ከትክክለኛው መንገድ የሳቱ አንዳንድ ሰዎች ኋላ ላይ በተግባራዊ ትምህርቶች ግሳጼ ወደ ልቦናቸው ይመለሳሉ፤ ነገር ግን ብዙዎች በልጅነት እና በወጣትነት ጊዜ ከፊል- የአንድ አቅጣጫን ዕድገት ስለ ተቀበሉ ለዘላለም ይጠፋሉ፡፡ ብልሹ ልጅ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ የሚሸከመው ከባድ ሸክም አለው፡፡ በመከራ፣ በተስፋ መቁረጥ፣ በፈተና ውስጥ የልተገራ፣ በተሳሳተ መንገድ የተመራ ፍላጎቱን ይከተላል፡፡ ታዛዥነትን ያልተማሩ ልጆች ደካማ እና ግልፍተኛ ባህሪዎች ይኖራቸዋል፡፡ ለመግዛት ይፈልጋሉ መገዛትን ግን አልተማሩም፡፡ አስቸጋሪ ስሜቶቻቸውን ለመቆጣጠር፣ መጥፎ ልማዶቻቸውን ለማስተካከል ወይም ከቁጥጥር ውጭ የሆኑ ፍላጎቶቻቸውን ለማስገዛት የግብረ ገብ ጥንካሬ የላቸውም። ያልሰለጠነ እና ያልተገረ የልጅነት ስህተት የጎልማሳ ወንድ እና ሴት ውርስ ይሆናል። የተጣመመው አዕምሮው በእውነት እና በሐሰት መካከል ያለውን ልዩነት ሊያስተውል የሚችለው አልፎ አልፎ ነው፡፡ 537Counsels to Parents, Teachers, and Students, 112, 113CGAmh 258.1

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents