Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents

የልጅ አመራር

 - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    ምዕራፍ 40—የክርስትና መርኾችን አርአያነት ያሳዩ

    ልጆች ከወላጆች ይኮርጃሉ— አባቶችና እናቶች፣ እናንተ መምህራን ናችሁ፤ ልጆቻችሁ ተማሪዎች ናቸው፡፡ የድምጻችሁ ቃና፣ ፀባያችሁ፣ መንፈሳችሁ፣ በትናንሽ ልጆቻችሁ ይኮረጃሉ፡፡ 403 The Signs of the Times, March 11, 1886.CGAmh 204.1

    ልጆች ከወላጆቻቸው ይኮርጃሉ፤ ስለሆነም ትክክለኛ አርአያነትን ለመስጠት ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ አለበት፡፡ ቤት ሩህሩህ እና ትሁት በተመሳሳይ ጊዜም ጽኑ እና ቆራጥ የሆኑ ወላጆች በልጆቻቸው ላይ ተመሳሳይ ባህሪዎችን ያያሉ፡፡ እነርሱ ቀና፣ ሐቀኛ እና ክቡር ከሆኑ ልጆቻቸው በዚህ ረገድ ከእነርሱ ጋር የመመሳሰል ዕድላቸው ሰፊ ይሆናል፡፡ እነርሱ እግዚአብሔርን የሚያከብሩ እና የሚያመልኩ ከሆነ በተመሳሳይ መንገድ የሰለጠኑት ልጆቻቸው እሱን ማገልገላቸውን አይረሱም፡፡ 404Testimonies For The Church 5:319, 320.CGAmh 204.2

    በቤተሰብ ውስጥ አባቶች እና እናቶች ልጆቻቸው እንዲኮርጁ የሚፈልጉትን አርአያነት ሁል ጊዜ ማሳየት አለባቸው፡፡ አንዳቸው ለሌላው በቃል፣ በአተያይ እና በድርጊት የፍቅር አክብሮት ማሳየት አለባቸው። የኢየሱስ ክርስቶስን ባህርይ ለልጆቻቸው በማሳየት መንፈስ ቅዱስ እነርሱን እየተቆጣጠረ እንደሆነ ማሳየት አለባቸው። የመኮረጅ ኃይል ጠንካራ ነው፤ ይህ ችሎታ ይበልጥ ንቁ በሚሆንበት በልጅነት እና በወጣትነት ጊዜ ፍጹም ምሳሌ በወጣቱ ፊት መቀረብ አለበት፡፡ ልጆች በወላጆቻቸው ላይ እምነት ሊጥሉ ይገባል፣ በመሆኑም በእነርሱ ውስጥ እንዲቀረጽ የሚፈልጉትን ትምህርት የሚወስዱት በዚህ መንገድ ነው ፡፡ 405The Review and Herald, March 13, 1894.CGAmh 204.3

    በመመሪያ እና በምሳሌ አስተምሩ— እናት ልጆቿን ስታስተምር ቀጣይነት ባለው ትምህርት ቤት ውስጥ ትሆናለች፡፡ ልጆቿን እያስተማረች እያለ ራሷ በየቀኑ ትማራለች፡፡ ልጆች ራሳቸውን እንዲገዙ የምትሰጣቸው ትምህርቶች በራሷ መተግበር አለባቸው፡፡ የልጆችን የተለያዩ አዕምሮዎች እና ስሜቶች ለመያዝ ጥልቅ ማስተዋል ያስፈልጋታል ወይም ልጆቿን አለአግባብ መፍረድ እና አድልኦን የመፍጠር አደጋ ላይ ትሆናለች፡፡ በቤት ውስጥ ህይወቷ ተግባራዊ ማድረግ ያለባት የርህራሄ ህግ ልጆቿ መልካም እና ሩህሩህ እንዲሆኑ የመመኘት መሆን አለበት፡፡ በየእለቱ በመመሪያ እና በምሳሌነት ትምህርቶች የሚደጋገሙት በዚህ መንገድ ነው፡፡ 406Pacific Health Journal, June, 1890CGAmh 204.4

    በትምህርት ቤት ውስጥ ያሉ አስተማሪዎች ልጆቻችሁን ለማስተማር አንድ ነገር ያደርጋሉ፣ ነገር ግን የእናነተ አርአያነት በማናቸውም ሌሎች መንገዶች ሊከናወን ከሚችለው በላይ ያደርጋል፡፡ ንግግራችሁ፣ የንግድ ሥራዎቻችሁን የምታስዳድሩበት መንገድ፣ የምትወዱትና የምትጠሉትን የምትገልጹበት ሁኔታ፣ ሁሉም ባሕርይን ለመቅረጽ ይረዳሉ፡፡ የርህራሄ ጸባይ፣ ራስን መግዛትን፣ ራስን መቆጣጠር፣ ልጅዎ በእናንተ ውስጥ የሚያየውን አክብሮት በየቀኑ ለእርሱ ትምህርት ይሆናል። እንደ ጊዜ፣ ይህ ትምህርት ሁል ጊዜም እየቀጠለ ነው፣ እናም የዚህ ዕለታዊ ትምህርት ቤት ዝንባሌ ልጃችሁ ወደፊት ምን መሆን እንዳለበት እየቀረጸው ነው። 407The Review and Herald, June 27, 1899.CGAmh 205.1

    ለልጆችዎ ትህትና የሌለው እንዳይሆኑ ተጠንቀቁ…፡፡ ታዛዥነትን እንደ መስፈርት ይጠይቁ፣ ለልጆችዎ በግዴለሽነት እንዲናገሩ ለራስዎ አይፍቀዱ፣ ምክንያቱም መልካም ምግባርዎ እና ቃላትዎ የትምህርቶቻቸው መጽሐፍ ናቸው፡፡ በዚህ የሕይወት ዘመናቸው ሁሉ በእርጋታ፣ በቀስታም ይርዷቸው፡፡ የመገኘትዎ ብርሃን በልባቸው ውስጥ ብርሃንን ይፍጠር፡፡ እነዚህ በማደግ ላይ ያሉ ወንዶች እና ሴቶች በጣም በቀላሉ ተጠቂ የሆነ ስሜት ያላቸው ናቸው፣ ኃይለኛ መሆንዎም መላ ህይወታቸውን ሊያበላሽ ይችላል፡፡ እናቶች ይጠንቀቁ፣ በጭራሽም አይቆጡ ምክንያቱም ይህ በጭራሽ አይጠቅምም፡፡6Manuscript Releases 12:7, 1898.CGAmh 205.2

    ወላጆች ራስን የመግዛት አርአያ መሆን አለባቸው— ልጆች በተቻለ መጠን ስሜታዊ ከመሆን መራቅ አለባቸው፤ በመሆኑም እናት ስሜታዊ ከመሆን እና ከጭንቀት ነፃ በመሆን መረጋጋት እና ጥድፊያ የሌላት መሆን አለባት። ይህ ለእራሷም ሆነ ለልጁ የሥነ— ምግባር ትምህርት ቤት ነው። ጨቅላዎችን ራስን የመካድን ትምህርት እያስተማረች እያለ፣ ለልጆቿ አርአያ እንድትሆን እራሷን እያስተማረች ነው። ተፈጥሮአዊ የኃጢያት ዝንባሌዎች ለማሸነፍ ርህራሄ በተሞላበት ዓላማ በልባቸው መሬት ላይ ስትሰራ፣ በገዛ ቃላቶቿ እና በገዛ ፀባይዋ ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋዎች እያሳደገች ነው። 408Manuscript Releases 4:3, 1900.CGAmh 205.3

    በእራስዎ ላይ የተቀዳጁት አንድ ድል ለልጆችዎ ትልቅ ዋጋ እና ማበረታቻ ይሆናል፡፡ እኔ የእግዚአብሔር እርሻ ነኝ፣ እኔ የእግዚአብሔር ሕንፃ ነኝ በማለት አመቺ መሰረት ላይ መቆም ይችላሉ፡፡ በጌታ መንገድ ላይ መጓዝ ይቀላቸው ዘንድ የልጆቼን አእምሮ እና ባህሪይ በማቅረጽ ከእግዚአብሔር ጋር አብሬ መሥራት እንድችል በመለኮታዊው ምሳሌ እንድቀረጽ ራሴን በእጁ ስር አስቀምጣለሁ፡፡ …አባቶችና እናቶች፣ እራሳችሁን ስትቆጣጠሩ ልጆቻችሁን በመቆጣጠር ታላላቅ ድሎችን ታገኛላችሁ፡፡ 409Letter 75, 1898CGAmh 206.1

    ራስን የመግዛት ፍሬዎች— ወላጆች፣ ራስን መቆጣጠር ሲያቅታችሁ እና ትዕግስት በማጣት በምትናገሩበት እና በምትተገብሩበት ጊዜ ሁሉ እግዚአብሔርን ትበድላላችሁ። መዝጋቢ መልአክ በፊታቸው የተነገሩ ትዕግስት የማጣት፣ ልቅ ቃላትን፣ ግድየለሽ ወይም ቀልድ፤ እያንዳንዱን ንጹህና ክቡር ያልሆነ ቃል በክርስትና ባህሪይህ ላይ እንደ ነቁጣ ይመዘግባል፡፡ ለልጆችዎ በርህራሄ ይናገሩ። ምን ያህል ስሜትዎ ይነካ እንደነበር፣ ወቀሳን ለመሸከም ምን ያህል ትንሽ እንደነበሩ ያስታውሱ፣ ስለሆንም እርስዎ መሸከም የማይችሉትን እነርሱ ላይ አይጫኑ፤ ምክንያቱም እነርሱ ከእርስዎ ይልቅ ደካሞች ስለሆኑ ያን ያህል መሸከም አይችሉም፡፡ ከእርስዎ የሚጠበቅ እራስን የመቆጣጠር፣ አሳቢነት እና ጠንቃቃነት መቶ እጥፍ ነው፡፡CGAmh 206.2

    ትሁት እና አስደሳች ቃላትዎ በቤተሰብዎ ውስጥ እንደ ፀሀይ ጮራ ይሁኑ፡፡ 410 The Signs of the Times, April 10, 1884. CGAmh 206.3

    ወላጆች ልጆቻቸው ቀና እንዲሆኑና እና የቀና ነገር እንዲያደርጉ ከፈለጉ፣ ራሳቸው በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር ቀና መሆን አለባቸው፡፡10Good Health, January, 1880.CGAmh 206.4

    ልጆች በክርስቲያን ነን ባዮች ባህሪይ ተጽዕኖ ያድርባቸዋል— ሰንበትን እንዲጠብቁ ከልጅነታቸው የተማሩ የሰንበት ጠባቂዎች ልጆች አሉ። ከእነዚህ ልጆች መካከል አንዳንዶቹ ከጊዜያዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በጣም ጥሩ ልጆች እና ለሥራ ታማኞች ናቸው፣ ነገር ግን የኃጢያት ጥልቅ የጥፋተኝነት ስሜት እና ከኃጢያት ንስሐ መግባት እንዳለባቸው የማይሰማቸው ናቸው። እንደነዚህ አይነቶቹ አደገኛ ሁኔታ ላይ ናቸው፡፡ እነርሱ ክርስቲያን ነን ባዮችን ባህሪይ እና ጥረታቸውን ይመለከታሉ፡፡ አንዳንዶች ከፍተኛ እውቀት ያላቸውን ነገር ግን ጠንቃቃ ያልሆኑ ክርስቲያኖችን ይመለከታሉ፣ እናም የራሳቸውን አመለካት እና ተግባር ከእነዚህ የመሰናክል ድንጋዮች ጋር ያነፃፅራሉ፤ በህይወታቸው ውስጥ ፈንድቶ የሚወጡ ኃጢያቶች ስለሌሉ ትክክል እንደሆኑ ራሳቸውን ያታልላሉ፡፡ 411 Testimonies For The Church 4:40.CGAmh 206.5

    ይህ የሆነበት ምክንያት የቅዱሳት መጻሕፍት ትምህርት በወጣቱ ላይ የበለጠ ተፅእኖ እንዳይኖረው ብዙ ወላጆች እና መምህራን የእግዚአብሄርን ቃል እንደሚያምኑ ሲናገሩ ህይወታቸው ኃይሉን የካደ በመሆኑ ነው፡፡ በተመሳሳይ ጊዜ ወጣቶች የቃሉ ኃይል እንዲሰማቸው ይደረጋሉ፡፡ የክርስቶስን ፍቅር ውድነት ይመለከታሉ። የእርሱን የባሕርይ ውበት፣ ማለትም ለአገልግሎቱ የተሰጡትን የህይወት ዕድሎች ይመለከታሉ። በአንፃሩ ግን የእግዚአብሔርን ሕግጋት እንደሚያከብሩ የሚናገሩ ሰዎችን ሕይወት ይመለከታሉ፡፡ 412 Education, 259.CGAmh 207.1

    ወላጆች ለፈተና “አይ” ማለት አለባቸው— እናቶች፣ የአለምን ልምዶች ባለመከተል፣ በልጆቻችሁ ፊት ለእግዚአብሔር ያላችሁን የታማኝነት ምሳሌ ማስቀመጥ፣ እንዲሁም አይሆንም እንዲሉ እነርሱን ማስተማር ትችላላችሁ፡፡ ለልጆቻቸው “ኃጢያተኞች ቢያባብሉህ እሺ አትበል” የሚለውን መመሪያ ትርጉም አስተምሯቸው፡፡ ነገር ግን ልጆችዎ ለፈተና አይሆንም እንዲሉ ከፈለጉ፣ እርስዎ እራስዎ እምቢ ማለት አለብዎ፡፡ ልጅ አይሆንም ማለት እንዳለበት ጎልማሳውም ሰው እንዲሁ ነው፡፡ 413The Review and Herald, March 31, 1891.CGAmh 207.2

    የጨዋነት ምሳሌነትን አሳዩ— ወላጆች፣ ለልጆቻችሁ ሩህሩህና ጨዋ ሁኑ፣ እነርሱም እንዲሁ ጨዋነትን ይማራሉ። እኛ ክርስቲያን መሆናችንን በቤታችን እናሳይ፡፡ በቤት ውስጥ ኑሮ በደግነት፣ በትዕግስት እና በፍቅር የማይተገበር ያንን ሙያ ዋጋ ቢስ እንደሆነ እቆጥረዋለሁ፡፡ 414Manuscript Releases 9:7, 1909.CGAmh 207.3

    የድምጽ እንዲሁም የቃላትን ቃና ይጠብቁ— አንድም የትዕግስት ማጣት፣ የማመናጨቅ ወይም የስሜታዊነት ቃል ከከንፈሮችዎ እንዳያመልጡ። የክርስቶስ ፀጋ መሻትዎን ይጠባበቃል፡፡ መንፈሱ ቃላትዎን እና ተግባሮችዎን በመምራት ልብዎን እና ህሊናዎን ይቆጣጠራል። በችኮላ እና ባልታሰቡበት ቃላት ክብሮን በጭራሽ አይጡ፡፡ ቃላትዎ ንፁህ፣ ንግግሮዎ ቅዱስ እንደሆኑ ይመልከቱ፡፡ ልጆችዎ እንዲሆኑ የሚፈልጉትን ምሳሌ ለልጆችዎ ያሳዩአቸው…፡፡ ሰላም፣ የትህትና ቃላት እና ደስተኛ ገጽታዎች ይኑሩ፡፡ 415 Letter 28, 1890.CGAmh 208.1

    ወላጆች በማናቸውም መንገድ ያለ ምንም አደጋ ሌሎችን የሚንቁ የበላይ መሆን አይችሉም፡፡ የጌታነትን፣ የትችት፣ የስህተት ፈላጊነት መንፈስ ማሳየት የለባቸውም፡፡ የሚናገሯቸው ቃላቶች፣ የሚናገሩበት ቃና፣ ለልጆቻቸው ለጥሩም ይሁን ለመጥፎ ትምህርቶች ናቸው፡፡ አባቶች እና እናቶች፣ ተቃራኒ ቃላት ከከንፈራችሁ ከወደቁ፣ ልጆቻችሁ በተመሳሳይ መንገድ እንዲናገሩ እያስተምሯቸው ነው፣ የመንፈስ ቅዱስም የማንጻት ተፅእኖ ዋጋ እንዳይኖረው ይደረጋል፡፡ ለልጆቻችሁ ያለባችሁን ኃላፊት ለመወጣት ብትፈልጉ በትዕግስት መልካም ማድረግን ማዘውተር አስፈላጊ ነው፡፡ 416Letter 8a, 1896.CGAmh 208.2

    ወላጆች ባህሪይ በመቅረጽ ውስጥ የእግዚአብሔር ወኪሎች ናቸው— የልጆቻችሁ አዕምሮዎች እየተቀረጹ ናቸው፣ ስሜቶች እና ባህሪያት እየተቀረጹ ናቸው፣ ነገር ግን ከየትኛው ንድፍ? ወላጆች በዚህ ሥራ ውስጥ ወኪሎች መሆናቸውን ያስታውሱ። በመቃብር ውስጥ በሚተኙበት ጊዜም ሥራቸው ጸንቶ ይቆያል፣ ስለ እነርሱም መልካምም ይሁን ክፉ ይመሰክራል፡፡ 417Pacific Health Journal, June, 1890.CGAmh 208.3

    መለኮታዊውን ምስል ማታም— አተያያችሁ፣ ቃላችሁ እና ተግባራችሁ በውዶቻችሁ የወደፊት ሕይወት ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንደሚኖራቸው በማስታወስ ማስተማር፣ ማስጠንቀቅ እና መምከር አለባችሁ፡፡ ሥራችሁ በሸራ ላይ የውበት ቅርጽን ለመቀባት ወይም ከእብነ በረድ ለመቅረጽ አይደለም፣ ነገር ግን የመለኮታዊውን ምስል በሰው ነፍስ ላይ ለመቅረጽ ነው፡፡ 418The Signs of the Times, May 25, 1882.CGAmh 208.4

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents