Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents

የልጅ አመራር

 - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    ምዕራፍ 78—የጸሎት ኃይል

    የቤተሰብ ጸሎት አስፈላጊነት— እያንዳንዱ ቤተሰብ እግዚአብሔርን መፍራት የጥበብ መጀመሪያ መሆኑን በመገንዘብ የጸሎት መሠዊያ መትከል አለበት። በዓለም ላይ ያሉ ማናቸውም ሰዎች ኃይማኖት የሚሰጠውን ጥንካሬ እና ማበረታቻ የሚፈልጉ ከሆነ፣ እነዚያ ለልጆች ትምህርትና ሥልጠና ኃላፊነት ያለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡ የየዕለቱ ምሳሌ መመሪያ ለማግኘት ወደ እነርሱ የሚመለከቱ ሰዎችን ያለ እግዚአብሔር መኖር እንደሚችሉ የሚያስተምሯቸው ሆኖ ሳለ ሥራቸውን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ባለው መንገድ መስራት አይችሉም፡፡ ልጆቻቸውን ለጊዜያዊ ሕይወት ብቻ እንዲኖሩ ካስተማሩ ለዘለዓለማዊነት ምንም ዓይነት ዝግጅት አያደርጉም፡፡ እነርሱ ያለ እግዚአብሔር እንደኖሩ ይሞታሉ፣ እናም ወላጆች ለነፍሳቸው መጥፋት ተጠያቂ ይሆናሉ። ወላጆች፣ እናቶች፣ ልጆቻችሁን በጥበብ፣ በርህራሄ እና በፍቅር እንዴት ማስተማር እንዳለባችሁ ለመማር በቤተሰብ መሠዊያ ላይ ጠዋት እና ማታ እግዚአብሔርን መሻት ይጠበቅባችኋል፡፡1037The Review and Herald, June 27, 1899.CGAmh 493.1

    የቤተሰብ አምልኮ ችላ ተብሏል— እያንዳንዱ ቤት የጸሎት ቤት መሆን ያለበት ጊዜ ቢኖር ያ ጊዜ አሁን ነው። አለማመን እና ክህደት ተስፋፍቷል፡፡ አመጽ በዝቷል፡፡ ብልሹነት በነፍስ ዋና ጅረቶች ውስጥ ይፈሳል፣ እናም በእግዚአብሔር ላይ ማመፅ ከህይወት ጥሶ ወጥቷል። የግብረ ገብ ኃይሎች በኃጢአት ባርነት ሥር በመሆን በሰይጣን አገዛዝ ሥር ናቸው፡፡ ነፍስ የእርሱ የፈተናዎች ስፖርት ሆኗል፤ እርሱንም ለማዳን አንድ ኃያል ክንድ ካልተዘረጋ በስተቀር ሰው ዋናው አመጸኛ ወደ መራው መንገድ ይሄዳል፡፡CGAmh 493.2

    ሆኖም ግን፣ በዚህ በሚያስፈራ አደገኛ ጊዜ ውስጥ ክርስቲያን ነን የሚሉ አንዳንድ ሰዎች የቤተሰብ አምልኮ የላቸውም፡፡ በቤት ውስጥ እግዚአብሔርን አያከብሩትም፤ ልጆቻቸው እርሱን እንዲወዱት እና እንዲፈሩት አያስተምሯቸውም፡፡ ብዙዎች እጅግ ከእርሱ ከመራቃቸው የተነሳ ወደ እርሱ ለመቅረብ ኩነኔ ስር ሥር እንዳሉ ይሰማቸዋል፡፡ እነርሱ “አለ ቁጣና አለ ክፉ አሳብ የተቀደሱትን እጆች እያነሱ፣” “ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት አይቀርቡም፡፡” 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፡8፤ ዕብራውያን 4፡16፡፡ ከእግዚአብሄር ጋር ህያው ግንኙነት የላቸውም፡፡ የኃይማኖት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን የሌላቸው ናቸው፡፡ 1038Testimonies For The Church 7:42.CGAmh 493.3

    ጸሎት አስፈላጊ አይደለም የሚለው ሀሳብ ነፍሳትን ለማጥፋት ከሰይጣን ከሚጠቀምባቸው እጅግ ስኬታማ ዘዴዎች አንዱ ነው፡፡ ጸሎት የጥበብ ምንጭ፣ የብርታት፣ የሰላም እና የደስታ ምንጭ ከሆነው ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት ማድረግ ነው፡፡ 1039Ibid.CGAmh 494.1

    የጸሎት-አልባ ቤት አሳዛኝ ሁኔታ— እንደ ጸሎት-አልባ ቤት ያህል ትልቅ ሀዘን የሚያደርስብኝን ሌላ ምንም ነገር አላውቅም። በእንደዚህ ዓይነት ቤት ውስጥ ለአንድ ሌሊት እንኳ ደህንነት አይሰማኝም፤ ደግሞም ወላጆች የሚፈለግባቸውን እና አሳዛኝ ቸልታቸውን እንዲገነዘቡ የመርዳት ተስፋ ባይኖረኝ ኖሮ እዚያ አልቆይም ነበር፡፡ እግዚአብሔርን መፍራት በፊታቸው ስላልሆነ ልጆቹ የዚህን ቸልተኝነት ውጤት ያሳያሉ፡፡ 1040The Signs of the Times, August 7, 1884.CGAmh 494.2

    ሥርዓቱን ለመጠበቅ ብቻ የሚደረግ ጸሎት ተቀባይነት የለውም— በብዙ ሁኔታዎች አንጻር የጠዋት እና የምሽት አምልኮ እንዲሁ ከመልክ ብቻ መሆን፣ ከለዛ ቢስነት በጥቂት ብቻ የሚበልጥ፣ የምስጋና መንፈስ ወይም የፍላጎት ስሜት የማይገለፅባቸው የተቀናበሩ ሐረጎች አሰልቺ እና ድግግሞሽ ብቻ ናቸው። ጌታ እንደዚህ አይነቱን አገልግሎት አይቀበልም። ነገር ግን የትሑታን ልብ እና የተጸጸተ መንፈስ ልመና አይናቅም። ለሰማያዊ አባታችን ልባችን መክፈት፣ ሙሉ በሙሉ ለምንደፍበት እውቅና መስጠት፣ የምንፈልጋቸው ነገሮች መግለጽ፣ የአመስጋኝነት ፍቅር ስግደት— ይህ እውነተኛ ጸሎት ነው።5The Signs of the Times, July 1, 1886.CGAmh 494.3

    የጸሎት ቤተሰቦች ይኑሩ— እንደ ጥንቱ አባቶች እግዚአብሔርን እንወዳለን የሚሉ ሁሉ ድንኳናቸውን በጣሉበት ቦታ ሁሉ ለጌታ መሠዊያ ማቆም አለባቸው…፡፡ አባቶች እና እናቶች ብዙውን ጊዜ ስለ ራሳቸው እና ስለ ልጆቻቸው በትህትና ተማጽኖ ልባቸውን ወደ እግዚአብሔር ከፍ ማድረግ አለባቸው፡፡ አባት፣ እንደ ቤተሰቡ ካህን፣ በጠዋት እና በማታ በእግዚአብሔር መሠዊያ ላይ መስዋእት ያቅርብ፣ ሚስት እና ልጆች በጸሎት እና በምስጋና ይተባበሩ፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ቤተሰብ ውስጥ ኢየሱስ ማረፍ ይወዳል፡፡ 1041Patriarchs and Prophets, 144.CGAmh 494.4

    የእያንዳንዱ ቤተሰብ አባላት ከሰማይ ጋር እጅግ እንደተጣመሩ ልብ ይበሉ። ጌታ እዚህ ታች ባሉት በልጆቹ ቤተሰቦች ላይ ልዩ ዓላማ አለው። መላእክት ለሚጸልዩ ቅዱሳን ጥሩ መዓዛ ያለው የእጣን ጭስ ያቀርባሉ፡፡ እንግዲያውስ በእያንዳንዱ ቤተሰብ ውስጥ በእኛ ፈንታ የአዳኙን ብቃት በእግዚአብሔር ፊት በማቅረብ በማለዳ እና በቀዝቃዛው የፀሐይ መጥለቂያ ሰዓት ጸሎት ወደ ሰማይ ያርግ። ማለዳ እና ማታ የሰማይ ሁለንተና የሚጸልየውን እያንዳንዱን ቤተሰብ ያስተውላል። 1042Manuscript Releases 19:1900.CGAmh 495.1

    መልአክቶች ለአምላክ በአደራ የተሰጡትን ልጆች ይጠብቋቸዋል— ለሥራ ከቤት ከመውጣታቸው በፊት ሁሉም ቤተሰቦች አንድ ላይ መጠራት አለባቸው፤ አባት ወይም አባት በሌለበት እናት ቀኑን ሙሉ እንዲጠብቃቸው እግዚአብሔርን አጥብቀው ይማጸኑ፡፡ በትህትና፣ በርህራሄ በተሞላ ልብ፣ እና በራሳችሁ እና በልጆቻችሁ ፊት ፈተናዎች እና አደጋዎች እንዳሉ በመረዳት፤ ስለ እነርሱ የጌታን እንክብካቤ በመማጸን በእምነት በመሠዊያው ላይ አኑሯቸው። በዚህ መልኩ ለእግዚአብሔር በአደራ የተሰጡ ልጆችን አገልጋይ መልአክት ይጠብቋቸዋል፡፡ 1043Testimonies For The Church 1:397, 398.CGAmh 495.2

    ጸሎት በልጆች ዙሪያ አጥር ይሠራል— ጠዋት ላይ የክርስቲያን የመጀመሪያ ሐሳብ በእግዚአብሔር ላይ መሆን አለበት፡፡ ዓለማዊ ሥራ እና ግላዊ ፍላጎት ሁለተኛ መሆን አለባቸው፡፡ ልጆች የጸሎትን ሰዓት እንዲያከብሩ መማር አለባቸው…፡፡ ክርስቲያን ወላጆች፣ ጠዋትና ማታ፣ በልባዊ ጸሎት እና በእምነት ጽናት፣ በልጆቻቸው ዙሪያ አጥር ማጠር ተግባራቸው ነው፡፡ በትዕግሥት ሊያስተምሯቸው ይገባል—እግዚአብሔርን ለማስደሰት እንዴት መኖር እንዳለባቸው በርህራሄ እና ያለመሰላቸት ሊያስተምሯቸው ይገባል። 1044Ibid.CGAmh 495.3

    ለአምልኮ የተወሰነ ጊዜ ይኑራችሁ— በእያንዳንዱ ቤተሰብ ውስጥ ለጧትና ማታ አምልኮ የሚሆን የተወሰነ ጊዜ ሊኖር ይገባል፡፡ ወላጆች የሰማያዊውን አባት በሌሊት ላደረገው ጥበቃ ለማመስገን እና በቀኑ የእርሱን እርዳታ፣ ምሪት እና የጥበቃ እንክብካቤ ለመጠየቅ ፆም ከመፈታቱ በፊት ልጆቻቸውን ወደ ራሳቸው መሰብሰብ ምንኛ ተገቢ ነው! በተጨማሪም ወላጆች እና ልጆች ምሽት ሲመጣ እንደገና በእርሱ ፊት ተሰብስበው ስላለፈው ቀን በረከቶች እርሱን ማመስገን ምንኛ ተገቢ ነው! 1045Testimonies For The Church 7:43.CGAmh 496.1

    በሁኔታዎች አትመሩ— የቤተሰብ አምልኮ በሁኔታዎች መመራት የለበትም፡፡ አልፎ አልፎ መጸለይ የለባችሁም፣ ደግሞም ሙሉ ቀን የሚያሰራችሁ ሥራ ሲገጥማችሁ ችላ በሉት። ይህንንም በማድረግ ልጆቻችሁ ጸሎት ምንም የተለየ ውጤት እንደሌለው እንዲቆጥሩ ትመሯቸዋላችሁ፡፡ ጸሎት ለእግዚአብሔር ልጆች በጣም ትልቅ ትርጉም አለው፣ የምስጋና መባዎችም ማለዳና ማታ ወደ እግዚአብሔር ፊት መምጣት አለባቸው፡፡ “ኑ፣ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን፣ ለአምላክ ለመድኃኒታችን እልል እንበል፡፡ በምስጋና ወደ ፊቱ እንድረስ፣ በዝማሬም ለእርሱ እልል እንበል፡፡” 1046Manuscript Releases 12:1898.CGAmh 496.2

    አባቶች እና እናቶች፣ ምንም እንኳን ሥራችሁ አስቸኳይ ቢሆን ቤተሰባችሁን በእግዚአብሔር መሠዊያ ዙሪያ ከመሰብሰብ ወደ ኋላ አትበሉ፡፡ የቅዱሳን መላእክት ጥበቃ በቤታችሁ ላይ እንዲሆን ጠይቁት፡፡ ውዶቻችሁ ለፈተናዎች የተጋለጡ መሆናቸውን አስታውሱ፡፡12The Ministry of Healing, 393.CGAmh 496.3

    ለእንግዶች ምቾት እና ደስታ በምናደርገው ጥረት ለእግዚአብሔር ያለንን ግዴታዎች ችላ ማለት የለብንም፡፡ የጸሎት ሰዓት ለማንኛውም ነገር ሥፍራ ለመስጠት ሲባል ችላ ሊባል አይገባም፡፡ ሁሉም በአምልኮው ሰዓት በደስታ ከመካፈል እጅግ እስኪዝሉ ድረስ በማውራት ራሳችሁንም አታስደስቱ፡፡ ይህንን ማድረግ አንካሳ መባን ለእግዚአብሔር ማቅረብ ነው፡፡ ያለ ችኮላ እና በማስተዋል መጸለይ በምንችልበት ገና አመሻሽ ሰዓት ላይ ልመናችንን ማቅረብ እና በደስታ እና በምስጋና ውዳሴ ድምፃችንን ማሰማት አለብን።CGAmh 496.4

    ክርስቲያኖችን የሚጎበኙ ሁሉ የጸሎቱ ሰዓት እጅግ የከበረ፣ እጅግ የተቀደሰ እና የቀኑ አስደሳች ሰዓት መሆኑን ያስተውሉ። እነዚህ የአምልኮ ሰዓታት በተካፋዮቹ ሁሉ ላይ የማንጻት፣ ከፍ የማድረግ ተጽዕኖ ማሳደር አለበት፡፡ እነርሱም ለመንፈስ ታላቅ የሆነ ሰላምን እና ዕረፍትን ያመጣሉ። 1047Messages to Young People, 342.CGAmh 497.1

    ልጆች የአምልኮ ሰዓትን መክበር አለባቸው— ልጆቻችሁ ደግ፣ ለሌሎች አሳቢ፣ ገር፣ በቀላሉ የሚለመኑ፣ እና ከምንም ነገር በላይ፣ ሃይማኖታዊ ነገሮችን ለማክበር እና የእግዚአብሔርን የይገባኛል ጥያቄዎች አስፈላጊነት እንዲገነዘቡ መማር አለባቸው። የጸሎትን ሰዓት እንዲያከብሩ መማር አለባቸው፤ በቤተሰብ አምልኮ ላይ ለመገኘት ጠዋት ላይ መነሳት ይጠበቅባቸዋል፡፡ 1048Testimonies For The Church 5:424.CGAmh 497.2

    የአምልኮውን ጊዜ ማራኪ አድርጉት— የቤተሰቡ ቄስ የሆነው አባት የጠዋቱን እና የማታውን አምልኮ መምራት አለበት። ይህ በቤት ሕይወት ውስጥ በጣም ማራኪ እና አስደሳች ተግባር የማይሆንበት ምንም ምክንያት የለም፣ ደግሞም እግዚአብሔር ይህ ደረቅ እና አሰልቺ በሚሆንበት ጊዜ አይከብርም። የቤተሰብ አምልኮ ወቅቶች አጭር እና መንፈሳዊ ይሁኑ፡፡ ልጆቻችሁ ወይም ማንኛውም የቤተሰባችሁ አባል አሰልቺ በመሆኑ ወይም በፍላጎት እጦት ምክንያት እንዲፈሩት አታድርጉ፡፡ አንድ ረዥም ምዕራፍ ሲነበብ እና ሲብራራ እና ረዥም ጸሎት ሲቀርብ ይህ ውድ አገልግሎት አሰልቺ ይሆናል፣ ሲያልቅም እፎይታ ይገኛል፡፡CGAmh 497.3

    የአምልኮ ሰዓቱን በከፍተኛ ሁኔታ አስደሳች ማድረግ የቤተሰቡ መሪዎች ልዩ ዓላማ መሆን አለበት፡፡ ወደ እግዚአብሔር ፊት ስንመጣ ለዚህ ጊዜ በትንሹ በማሰብ እና በጥንቃቄ በመዘጋጀት፣ የቤተሰብ አምልኮ አስደሳች እና ዘላለማዊነት ብቻ በሚገልጣቸው ውጤቶች የተሞላ ይሆናል። አባት አስደሳች እና በቀላሉ መረዳት የሚቻለውን የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍል ይምረጥ፤ በቀን ውስጥ ሊጠና እና መለማመድ የሚችል ትምህርት ለማቅረብ ጥቂት ጥቅሶች በቂ ናቸው። ጥያቄዎች ሊጠየቁ ይችላሉ፣ ጥቂት ልባዊ፣ አስደሳች አስተያየቶች ወይም ክስተቶች አጭር እና ጉዳዩ ላይ ያተኮረ በመሆን በምሳሌ ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡ ቢያንስ ጥቂት መንፈሳዊነት ያላቸው መዝሙሮች ሊዘመሩ ይችላሉ፣ ደግሞም የሚቀርበው ጸሎት አጭር እና ነጥቡ ላይ ያነጣጠረ መሆን አለበት። በጸሎት የሚመራ ሰው ስለ ሁሉም ነገር መጸለይ የለበትም፣ ነገር ግን ፍላጎቶቹን በቀላል ቃላት መግለፅ እና እግዚአብሔርን በምስጋና ማክበር አለበት፡፡ 1049The Signs of the Times, August 7, 1884.CGAmh 497.4

    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፍቅርን ለመቀስቀስ እና ለማጠናከር በብዛት በአምልኮው ሰዓት ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጠዋት እና የምሽት አምልኮ ሰዓቶች ከቀኑ በጣም ጣፋጭ እና በጣም አጋዥ መሆን አለባቸው። በእነዚህ ሰዓታት ውስጥ ምንም ችግር ያለበት፣ ርህራሄ የጎደለው አስተሳሰብ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፤ ወላጆች እና ልጆች ከኢየሱስ ጋር ለመገናኘት እና የቅዱሳን መላእክት መገኘት መጋበዝ እንዳለባቸው ይገንዘቡ፡፡ አገልግሎቶቹ አጭር እና በህይወት የተሞሉ፣ ከወቅቱም ጋር የሚስማሙ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ የተለያዩ ይሆኑ። ሁሉም በመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ውስጥ በመሳታፍ ይማር፣ ብዙውን ጊዜም የእግዚአብሔርን ሕግ ይደግሙ። አንዳንድ ጊዜ ንባቡን እንዲመርጡ ከተፈቀደላቸው የልጆችን ፍላጎት ይጨምራል፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ ጥያቄ ጠይቋቸው፣ እነርሱም ጥያቄዎችን ይጠይቁ፡፡ ትርጉሙን ለማብራራት የሚያገለግል ማንኛውንም ነገር ጥቀሱ፡፡ ስለዚህ አገልግሎቱ በጣም ረዥም በማይሆንበት ጊዜ፣ ትንንሾቹ ልጆች በጸሎት ይሳተፉ፣ አንድ ነጠላ ጥቅስ ብቻ ከሆነም በመዝሙሩ ይቀላቀሉ፡፡ 16Education, 186.CGAmh 498.1

    ግልፅ እና ልዩ ፀሎት አቅርቡ— ምሳሌ በመሆን ልጆቻችሁን ግልፅ፣ ልዩ ፀሎት እንዲያቀርቡ አስተምሯቸው፡፡ ጭንቅላታቸውን ከወንበሩ ላይ ማንሳት እንዳለባቸው እና በጭራሽ ፊታቸውን በእጆቻቸው መሸፈን እንደሌለባቸው አስተምሯቸው፡፡ በዚህ ሁኔታ የጌታን ጸሎት በሕብረት በመድገም ቀለል ያሉ ጸሎቶቻቸውን ማቅረብ ይችላሉ፡፡ 1050Manuscript Releases 12:1898.CGAmh 498.2

    የሙዚቃ ኃይል— የመጽሐፍ ቅዱስ መዝሙሮች ታሪክ በሙዚቃ እና በመዝሙር አጠቃቀም እና ጥቅሞች አስተያየት የተሞላ ነው፡፡ ሙዚቃ ብዙውን ጊዜ ክፉ ዓላማዎች ላይ ለመዋል ፈሩን ይለቃል፣ በዚህም መንገድ እጅግ በጣም አታላይ ከሆኑ የፈተና መሳሪያዎች አንዱ ይሆናል። ነገር ግን በትክክል ሥራ ላይ የዋለ እንደሆነ አስተሳሰቦችን ወደ ከፍተኛ እና ክቡር ጭብጦች ከፍ ለማድረግ፣ ነፍስን ለማነቃቃት እና ከፍ ለማድረግ የታለመ የእግዚአብሔር ውድ ስጦታ ነው…፡፡CGAmh 499.1

    ልብን በመንፈሳዊ እውነት ለመንካት በጣም ውጤታማ ከሆኑ መንገዶች አንዱ ነው፡፡ የተጨነቀች እና ተስፋ ለመቁረጥ ዝግጁ የሆነች ነፍስ ስንት ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል— ለረጅም ጊዜ የተረሳው የልጅነት የመዝሙር ሸክም ስታስታውስ— ፈተናዎች ኃይላቸውን ያጣሉ፣ ሕይወት አዲስ ትርጉም እና አዲስ ዓላማን ይይዛል፣ እንዲሁም ድፍረትን እና ደስታን ለሌሎች ነፍሳት ይሰጣል!CGAmh 499.2

    እንደ አንዱ የትምህርት መሣሪያ የመዝሙር ዋጋ በጭራሽ መዘንጋት የለበትም፡፡ ቤት ውስጥ ጣፋጭ እና ንፁህ ዝማሬዎች ሲዘመሩ የዘለፋ ቃላት ይቀንሱ እና ይበልጥ የደስታ እና የተስፋ ቃላት ይኖራሉ። በትምህርት ቤት ውስጥ መዝሙር ይኑር፤ እና ተማሪዎች ወደ እግዚአብሔር፣ ወደ አስተማሪዎቻቸው እና ወደ እርስ በእርስ ይበልጥ ይቀርባሉ፡፡CGAmh 499.3

    እንደ አንድ የሃይማኖት አገልግሎት አካል መዝሙር እንደ ጸሎት ሁሉ የአምልኮ ተግባር ነው፡፡ በእርግጥ ብዙ መዝሙር ጸሎት ነው፡፡ ልጅ ይህንን እንዲገነዘብ ከተማረ እርሱ ስለሚዘምራቸው ቃላት ትርጉም የበለጠ በማሰብ ለኃይላቸው ይበልጥ የሚማረክ ይሆናል።18Education, 167, 168.CGAmh 499.4

    መሳሪያ እና ድምጽ— ምሽት እና ማለዳ ከልጆቻችሁ ጋር በእግዚአብሔር አምልኮ ላይ ቃሉን በማንበብ እና ስለ እርሱ ውዳሴ በመዘመር ተካፋይ ሁኑ። የእግዚአብሔርን ሕግ እንዲደጋግሙ አስተምሯቸው፡፡ ትዕዛዛቱን በተመለከተ “ለልጆችህም አስተምረው፣ በቤትህም ስትቀመጥ፣ በመንገድም ስትሄድ፣ ስትተኛም፣ ስትነሳም ተጫወተው” ሲል እስራኤላውያን አዝዞ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ሙሴ የሕጉን ቃላት በሙዚቃ እንዲያዘጋጁ እስራኤላውያንን አዘዛቸው፡፡ ትልልቅ ልጆች መሳሪያዎችን ሲጫወቱ ታናናሾቹም የእግዚአብሔርን ትእዛዛት በሕብረት በሰልፍ ይጓዛሉ፡፡ በኋለኞቹ ዓመታት በልጅነት ጊዜ የተማሩትን የሕግ ቃላትን በአእምሯቸው ውስጥ ያስቀርሉ፡CGAmh 499.5

    በምድረ በዳ በሚጓዙበት ጊዜ ልጆች ሕጉን ቁጥር በቁርጥ መማር ይችሉ ዘንድ ሙሴ ትእዛዛቱን በቅዱስ መዝሙር ማካተቱ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በዚህ ወቅት ልጆቻችንን የእግዚአብሔርን ቃል ማስተማር ምን ያህል አስፈላጊ ነው! ልጆቻችን ትእዛዛቱን ቃል በቃል እንዲጠብቁ እያስተማርን ለእርዳታ ወደ ጌታ እንምጣ። እግዚአብሔር ወደ ቤታችን ይገባ ዘንድ በቻለን መጠን ቤታችን ውስጥ ሙዚቃ እንዲኖር እናድርግ፡፡ 1051Evangelism, 499, 500.CGAmh 500.1

    ልዩ የአምልኮ ጊዜ ለሰንበት— በቤተሰብ የአምልኮ ጊዜ [በሰንበት] ልጆች ተሳትፎ ይኑራቸው፡፡ ሁሉም መጽሐፍ ቅዱሶቻቸውን ይዘው ይምጡ እና እያንዳንዱ አንድ ወይም ሁለት ጥቅስ ያነብቡ፡፡ ከዚያ ጸሎትን ተከትሎ የተወሰኑ የታወቁ መዝሙሮች እንዲዘመሩ አድርጉ። ለዚህም ክርስቶስ ሞዴል ሆኗል፡፡ የጌታ ጸሎት ለሥርዓቱ ብቻ እንዲደጋገም የታሰበ ሳይሆን ጸሎታችን ምን መሆን እንዳለበት— ማለትም ቀላል፣ ልባዊ እና ሁሉን አቀፍ መሆንን የሚያሳይ ተምሳሌት ነው። ቀላል ባለ ልመና ለጌታ ፍላጎታችሁን ንገሩት እና ስለ ምህረቱ አመስጋኝነትን ግለጹለት፡፡ በዚህም መንገድ ኢየሱስን በቤታችሁ እና በልባችሁ ውስጥ እንደ ተወዳጅ እንግዳ አድርጋችሁ ትጋብዙታላችሁ። በርቀት ያሉ ነገሮችን በተመለከተ በቤተሰብ ውስጥ ረዥም ጸሎቶች መቅረብ የለባቸውም፡፡ እነዚህ ነገሮች እንደ ዕድል እና በረከት መቆጠር ሲችሉ የጸሎትን ሰዓትን አድካሚ ያደርጉታል። ጊዜውን ማራኪና እና አስደሳች አድርጓት፡፡ 1052Testimonies For The Church 6:357, 358.CGAmh 500.2

    ብዙ ጸሎት አነስተኛ ቅጣት ማለት ነው— ከዚህ በፊት ከምናደርገው በላቀ ሁኔታ ወደ እግዚአብሔር መጸለይ አለብን። በቤተሰቦቻችን ውስጥ፣ ከልጆቻችን ጋር እና ስለ ልጆቻችን በመጸለይ ታላቅ ጥንካሬ እና በረከት አለ። ልጆቼ ስህተት ሲፈጽሙ፣ እና በርህራሄ ከእነርሱ ጋር ተነጋግሬ ከእነርሱ ጋር ከጸለይኩ በኋላ እነርሱን መቅጣት ከዚያ በኋላ አስፈላጊ ሆኖ አላገኘውም፡፡ ለጸሎት ምላሽ በመጣው መንፈስ ቅዱስ ልባቸው በርህራሄ ይቀልጣል፡፡ 1053Manuscript Releases 4:7, 1908.CGAmh 500.3

    የግል ጸሎት ጥቅሞች— ኢየሱስ በግል በሚጸልይበት ሰዓታት ውስጥ ነበር በምድር ሕይወት ላይ ጥበብ እና ኃይል የተቀበለው፡፡ ወጣቶች ከሰማይ አባታቸው ጋር ለመገናኘ በማለዳ እና በምሽት ፀጥ ያለ ጊዜ በመፈለግ የእርሱን ምሳሌ ይከተሉ። ደግሞም ቀኑን ሙሉ ልባቸውን ወደ እግዚአብሔር ያንሱ፡፡ እርሱ በመንገዳችን በእያንዳንዱ እርምጃ ላይ “እኔ አምላክህ እግዚአብሔር እረዳሃለሁ ብዬ ቀኝህን እይዛለሁና... አትፍራ፡፡” (ኢሳይያስ 41:13) ይላል፡፡ ልጆቻችን በዕድሜያቸው ማለዳ ላይ እነዚህን ትምህርቶች መማር ቢችሉ ኖሮ፣ እንዴት ያለ መታደስ እና ኃይል፣ እንዴት ያለ ደስታ እና ጥሩነት በሕይወታቸው ላይ ይመጣ ነበር!22Education, 259.CGAmh 501.1

    የሰማይ በሮች ለእያንዳንዱ እናት ክፍት ናቸው— ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ በዮርዳኖስ ዳርቻ ላይ ሰግዶ ለሰው ልጆች ሲጸልይ ሰማያት ተከፈቱ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ የሚያብረቀርቅ የወርቅ ርግብ የሚመስል የአዳኝን መልክ ከበው ነበር፤ “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው” የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ።CGAmh 501.2

    ይህ ለእናንት ምን ትርጉም አለው? ለፀሎታችሁ ሰማይ ክፍት እንደሆነ ይናገራል፡፡ በተወዳጁ ዘንድ ተቀባይነት እንዳገኛችሁ ይናገራል፡፡ በአዳኝ እግር ስር ሸክሟን ለማራገፍ ለምትሻ እናት ሁሉ በሮች ክፍት ናቸው፡፡ ክርስቶስ የሰውን ልጅ በክንዱ እንደሚያቅፍ፣ በመለኮታዊ ክንዱም ወሰን የሌለውን ዙፋን በመያዝ ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር፣ ምድርንም ከሰማይ ጋር እንዳቆራኘ ይናገራል፡፡ The Signs of the Times, July 22, 1889. 1054The Signs of the Times, July 22, 1889.CGAmh 501.3

    የክርስቲያን እናቶች ጸሎት አንድን ህዝብ ለራሱ ቤዛ ለማድረግ ልጁን ወደ ምድር በላከው የሁሉም አባት ችላ አይባልም፡፡ በታላቁ ቀን የፍጻሜ ተጋድሎ ላይ ልመናችሁን ችላ በማለት እናንተን እና የእናንተ የሆኑትን ለሰይጣን መጨወቻ ይሆኑ ዘንድ አይተዋችሁም፡፡ እናንተ ቀላል በሆነ ሁኔታ እና በታማኝነት እንድትሠሩ ይፈለግባችኋል፣ እግዚአብሔርም የእጆቻችሁን ሥራ ያጸናል። 1055The Review and Herald, April 23, 1889.CGAmh 501.4

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents