Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents

የቤተ ፡ ክርስቲያን፡ ምክሮች፡፡

 - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First

    ክርስቶስ ብቻ በሰው ሊፈርድ ይችላል፡፡

    ክርስቶስ ሰው ሊጋጠመውና ይችለው ዘንድ የሚገባውን ፈተናዎችን ለመጋጠምና ለመቻል የሰው ራስ ሆኖ ይቆም ዘንድ ራሱን አዋረደ፡፡ የተፈተኑትን እንደምን ለመርዳት እንዲያውቅበት ሰው ከወደቀው ጠላት የሚሠነዘርበትን ለመጋጠም ያለበትን ሁናቴ እርሱ ማወቅ ሆነበት፡፡CCh 123.5

    ክርስቶስ ፈራጃችን ሆኖአል፡፡ አብ ፈራጅ አይደለም፤ መላእክትም አይደሉም፡፡ በራሱ ላይ የሰውን አካል የለበሰና በዚህ ዓለም ፍጹም የሆ ሕይ ወት የኖረ ሊፈርድብን ነው፡፡ እርሱ ብቻ ፈራጃችን ሊሆን ይችላል፡፡ ይህን ትዝ ይላችኋልን ወንድሞቼወ ታስታውሱታላችሁን እናንተም ሰሳኮች አባቶችና እናቶች የሆናችሁም ታስታውሱታላችሁንታ ክርስቶስ ፈራጃችን ይሆን ዘንድ የሰውን አካል ለበሰ በሌላ ላይ ፈራጅ ይሆን ዘንድ ከናንተ ማነም የተሾመ የለም፡፡ ራሳችሁን በዲሲፕሊን ለማሠልጠን የምትችሉት ይኸው ብቻ ነው፡ እንግዲህ በክርስቶስ ስም የምለምናችሁ በፍርድ ወንበር ከቶውን እንዳትቀመጡ የሚሰጣችሁን ቃል እንደትቀበሉ ነው፡፡ ቀን በቀን ይህ መልእክት በጆሮቼ ተሰምቷል፤ ‹‹ከፍርድ ወንበር ውረድ በትህትና ውረድ››፡፡ ፲109T185, 186;CCh 123.6

    እግዚአብሔር ኃጢአቶች ሁሉ በታላቅነታቸው እኩል ለኩል እንደሆኑ አይመለከትም ውስን በሆነው በሰው ግምትም ሆነ በርሱ ግምት በኃጢአት ደረጃዎች አሉ፡ ነገር ግን በሰዎች አይኖች ዘንድ ይህ ወይም ያ ስህተት ደረጃዎች አሉ፡፡ ነገር ግን በሰዋች ዓይኖች ዘንድ ይህ ወይም ያ ስህተት በአኳናቸው ምንም ቀላል ሆኖ ቢመስላቸው በአምላክ ፊት ኃጢአት ትንሽ አይደለም፡፡ ሰው ትንንሾች እንደሆኑ ለመመልከት የሚቃጣ ኃጢአቶች ታላላቅ ወንጀሎች እንደሆኑ የሚቆጥራቸው ይሆናሉ፡ ትዕቢት ራስን መውድድና ስስት ሳይዘለፉ ቀርተው ሰካራም የተናቀና ኃጢአቱ ከሰማይ የሚያስወግደው እንደሆነ ይነገራል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ኃጢአቶች በአምላክ ዘንድ በተለይ የተጠሉ ናቸው፡፡ እርሱ፤ ‹ትዕቢተኛውን ይቃወማል›፤ ጳውሎስም ስስት ጣዖተ አምልኮ እንደሆነ ይነግረናል፡፡ በአምላክ ቃል ውስጥ ስለ ጣዖተ አምልኮ የተሰጡትን ዘለፋዎች የማያውቁ፤ ይህ ኃጢአት እንደምን በጣም የሚጠላ መሆኑን ባንድ ጊዜ ያያሉ፡፡ ፲፩115T337.CCh 124.1