Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents

የቤተ ፡ ክርስቲያን፡ ምክሮች፡፡

 - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First

    በቤተ ክርስቲያን ላሉት ድሆች የምናደርገው ተግባራችን፡፡

    ሁልጊዜ በዳርቻዎቻችን ውስጥ ያሉን ሁለት የድሆች አሉ እነዚህም በገዛ የስድ አድራጎታቸው እርምጃ ራሳቸውን የሚያጠፉና ሕግን በመተላለፍ የሚቀጥሉና ለእውነት ሲሉ ከችግር ሁኔታ ውስጥ የገቡ ናቸው፡፡ እንደ ራሳችን ባልንጀራንን መውደድ አለብን፤ በዚያን ጊዜ በዓይነተኛ ጥበብ መሪነትና ምክር መሠረት ለእነዚህ ሁለቱ ክፍሎች የቀና ነገር እናደርጋለን፡፡CCh 126.3

    ስለ ጌታ ድሆች የሚቀርበው ጥያቄ የለም፡፡ለጥቅማቸው.................CCh 126.4

    ................ ዓለም እንዲገልጹ ሕዝቡን ይፈልጋል፡፡ ለእውነት ሲሉ ከቤቶቻቸው ተነጥለው ለመቸገር የሚገደዱትን ለመርዳት የተለየ ልፋት ሊደረግላቸው ይገባል፡፡ ሰፋ ያለ ልበ ክፍት ለጋሶች ልቦች ያሏቸውን ራስን የሚክዱና አምላክ የሚወዳቸውን የነዚህኑ ሰዎች ጉዳይ የሚያከባክቡላቸው በይበልጥ የሚያስፈልጉ ናቸው፡፡ በእግዚአብሔር ሕዝብ መኻከል ያሉትን ድሆች ለፍላጎታቸው ያለ ስንቅ ሊተውዋቸው አይገባቸውም፡፡ ለኑሮዋቸው የሚሆነውን ሊያገኙ የሚችሉበት አንድ መንገድ ሊገኘላቸው ተገቢ ነው፡፡ አንዳንዶች ለመሥራት መማር ያስፈልጋቸዋል፡ ሌሎችም ቤተሰቦቻቸውን ለመደገፍ ጠንክረው የሚሠሩና በተቻላቸው ዓቅም የሚለፉ የተለየ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ለኒህ ጉዳዮች ማሰብና ሥራ እንዲያገኙ ልንረዳቸው አለብን፡፡ አምላክን የሚወዱና ትእዛዛቱን የሚጠብቁትን ተገቢዎች የሆኑትን ድሆች ቤተሰቦች ለመርዳት ተቀማጭ ገንዘብ ሊኖር ይገባል፡፡CCh 126.5

    እግዚአብሔርን የሚወዱና የሚታዘዙት ባንዳንድ ሁኔታዎች የተነሣ ድሆች ይሆናሉ፡፡አንዳንዶቹ ጥንቁቆች አያደሉም የኑሮን አያያዝ አያውቁበትም፡፡ ሌሎችም በበሽታና ባለመታደል የተነሣ ድሆች ይሆናሉ፡፡ ምክንያቱም ምንም ይሁን እነሱ በችግር ላይ ናቸውና፤ እነሱን መርዳት ዋና /ጠቃሚ/ የሆነ ወንጌላዊ ሥራ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በተቋቋመችበት ሥፍራ ሁሉ አባሎቿ ለችግረኞች ምዕመናን የታመነ ሥራ መሥራት አለባቸው፡፡ ነገር ግን እዚሁ ላይ መቆም የለባቸውም፡፡ ኃይማኖታቸውን ሳይመለከቱ ሌሎችን ደግሞ መርዳት ይኖርባቸዋል፡፡ በእንዲህ ያለ ጥረት የተነሣ፤ ለዚህ ጊዜ የሚሆነውን የተለየ እውነት ከነዚሁ አንዳንዶቹ ይቀበላሉ፡፡ ፯76T- 269-271;CCh 126.6