Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents

የክርስቲያን አገልግሎት

 - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    ፋይዳ ቢሶቹ የሥነ ምግባር መምህራን

    ራሳቸውን ክርስቲያን ብለው ከሚጠሩ መካከል አብዛኞቹ ከሰብዓዊ የሥነ ምግባር መምህርነት የዘለለ ፋይዳ የላቸውም፡፡ ክርስቶስን በዚህ ዓለም በመወክል ለእርሱ ክብር ለመስጠት የሚያስችላቸውን ብቸኛውን ስጦታ ተቃውመዋል፡፡ ቃሉን አድራጊዎች ላልሆኑት ለእነርሱ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ እንግዳና ያልተለመደ ነው፡፡ ከክርስቶስ ጋር በአንድነት የሆኑትን እና በዓለም ያሉትን ለይተው የሚያሳዩት ሰማያዊ መርኅዎች ይህን ማድረግ በማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል፡፡ የክርስቶስ ተከታዮች ከሌሎች የተለዩና ልዩ ጠባይ ያላቸው ሕዝቦች የመሆናቸው ጉዳይ ያበቃለት ይመስላል፡፡እነዚህን ሁለቱን የሚለየው መስመር ደብዛዛና የማይታይ ሆኖአል፡፡ ሕዝቡ ራሱን ለዓለማዊ ልማዶች፣ ወጎችና ራስ ወዳድነት እያስገዛ ይገኛል፡፡ ዓለም ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥቶ ሕጉን መታዘዝ ሲገባው ቤተ hርስቲያን ሕጉን ተላልፋ ዓለም ውስጥ ገብታለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን በየቀኑ ዓለምን እየመሰለች በመለወጥ ላይ ትገኛለች፡፡-Christ’s Object Lessons, pp. 315, 316. ChSAmh 60.2

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents