Loading...
Larger font
Smaller font
Copy
Print
Contents

የክርስቲያን አገልግሎት

 - Contents
  • Results
  • Related
  • Featured
No results found for: "".
  • Weighted Relevancy
  • Content Sequence
  • Relevancy
  • Earliest First
  • Latest First
    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents

    መንፈሳዊ ልፍስፍስነት

    ልምምድን ተከትሎ _ ብርታትና _ ጥንካሬ ይገኛል፡፡ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ተሰጥኦ የሚጠቀሙ ሁሉ ለአገልግሎቱ ሊያውሉ የሚችሉት ላቅ ያለ ችሎታ አላቸው፡፡ ለአምላካዊው አገልግሎት አንዳችም ድርሻ የማያበረክቱ በጸጋም ሆነ በእውነት ዕውቀት ከማደግ ይገታሉ፡፡ ያለ ሥራ ከመቀመጥ ውጪ እጅና እግሮቹን ለማንቀሳቀስ ፈቃደኛ የማይሆን ሰው ውሎ አድሮ ሊጠቀምበት ይችል የነበረውን ጉልበት ያጣል፡፡ በዚህ የተነሳ ክርስቲያኑ ሥራ ላይ እንዲያውለው በእግዚአብሔር የተሰጠውን ጉልበት ጥቅም ላይ ባለማዋሉ በክርስቶስ እንዳያድግ መገታት ብቻ ሳይሆን ነገር ግን የነበረውንም ተሰጥኦ የመጠቀም ኃይል በማጣት የመንፈሳዊ ልፍስፍስነት ተጠቂ ይሆናል፡፡ ለእግዚአብሔርና ለባልንጀራቸው ፍቅር ያላቸው፣ በዐለቱ ላይ የተመሰረቱ፣ የጠነከሩና በእውነት ላይ ተደላድለው የተቀመጡ፤ ሌሎችን ለመርዳት ብርቱ ትግልና ጥረት ያደርጋሉ፡፡ እውነተኛ ክርስቲያን በስሜት ተገፋፍቶ ለአንድ ቀን ወይም ለአንድ ወር አይሠራም፡፡ ይልቁንም አምላካዊውን መርኅ መሰረት አድርጎ ሕይወቱን ሙሉ እግዚአብሔርን ያገለግላል፡፡Testimonies, vol. 5, p. 393. ChSAmh 147.1

    Larger font
    Smaller font
    Copy
    Print
    Contents